Saturday, February 29, 2020

የዕለተ ቅዳሜ ከሰዓት ስፖርታዊ ዜናዎች

አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)



አወዛጋቢው የናፖሊ ፕሬዝደንት ኦላሪዮ ደ ላውረንቲስ የኻሊዱ ኩሊባሊ መ'ሸጫ ዋጋ €99ሚ. እንዲሆን ወስነዋል።ሴኔጋላዊው ድንቅ ተከላካይ በበርካታ ሐያላን የአውሮፓ ክለቦች የሚፈለግ ሲሆን ከፈላጊዎቹ መሀከል ማንቸስተር ዩናይትድ ፣ ፒ.ኤስ.ጂ ፣ ባርሴሎና ፣ ሪያል ማድሪድ እና ማንቸስተር ሲቲ ይገኙበታል።
(Mail Online)




ፍራንክ ላምፓርድ ቋሚ ተሰላፊ እንደሚያደርገው ዋስትና ስላልሰጠው ፥ ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባልጋ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት ቼልሲን ለመልቀቅ ወስኗል።
(Mail)





የማንቸስተር ዩናይትዱ አለቃ ኦሌ ጉናር ሶልሻየር መልማዮችን ወደ ጣሊያን ልኳል።ሶልሻየር የላካቸው መልማዮች ተግባርም £60ሚ. የሚገመተውን የፍዮረንቲናውን የክንፍ አጥቂ ፌዴሪኮ ቼሳ በሜዳ ተገኝተው አቋሙን እንዲመለከቱ ነው።
(Mail)





የጀርመናዊው አማካይ ሜሱት ኦዚል ወኪል እንደተናገረው ከሆነ የ31 አመቱ ተጨዋች ውሉ እስኪጠናቀቅ ማለትም እስከ 2021 መድፈኞቹን ሳይለቅ በኤምሬትስ ይቆያል።
(inews)





የቀድሞው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አምበል ዴቪድ ቤካም ፖርቱጋላዊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ከአርጀንቲናዊው ሊዮኔል ሜሲ እሱ በባለቤትነት በያዘው ኢንተር ሚያሚ ቢመጡ ደስተኛ እንደሚሆን ተናግሯል።
(ESPN)




መነሻው ቻይና የነበረው እና በአሁኑ ሰዓት በርካታ ሀገራት ላይ እየተስፋፋ የሚገኘው ኮሮና ቫይረስ በብዙ ሊጎች ላይ ስጋትን ደቅኗል።በዚህ ሳምንት ከግማሽ በላይ የጣሊያን ሴሪ ኤ ጨዋታዎች በዝግ ሜዳ የሚደረጉ ሲሆን ይህ ነገር ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግም ሊመጣ ይችላል።
(Telegraph)




ጁቬንትስ የማንቸስተር ሲቲውን ብራዚላዊ አጥቂ ጋብሬል ጄሱስ የማዘዋወር ፍላጎት አለው።የአሮጊቷ ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ፋቢዮ ፓራቲቺ ከጓዶቻቸው ጋር የ22 አመቱን ተጨዋቾ ዕድገት ሲከታተሉ የሰነበቱ ሲሆን ክረምት ላይም ለማዘዋወር አቅደዋል።ጄሱስ በዘንድሮው አመት በሁሉም የውድድር አይነቶች በ36 ጨዋታዎች 18 ግቦችን ከመረብ አሳርፏል።
(Calcio Mercato)





አትሌቲኮ ማድሪድ የዊልያንን እና የቼልሲን ጉዳይ በአጽንኦት በመመልከት ላይ ይገኛል።ዲያጎ ሲሞኑ ብራዚላዊው አጥቂ በቼልሲ ውሉን ካላራዘመ በነጻ ዝውውር ወደ ዋንዳ ሜትራ ፖሊታኖ እንዲመጣለት ይሻል።ባርሴሎና እና ቶተንሃምም የዊልያን ፈላጊዎች ናቸው።
(Tuttomercatoweb)





Friday, February 28, 2020

የምንጊዜም የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ምርጥ 20 ተጨዋቾች

የምንጊዜም የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ምርጥ 20 ተጨዋቾች

              አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)


ስመ ጥሩ ጋዜጣ ፎር ፎት ቱ ከሰሞኑ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ታሪክ የታዩ ምርጥ 100 ተጨዋቾችን በአያሌ መመዘኛዎች መዝኖ ይፋ አድርጓል።እኛም ከ1-20 ያሉትን እንደሚከተለው አሰናድተናል።



20.ፒተር ሽማይክል


19.ቨንሶ ኮምፓኒ


18.ዴኒስ ቤርካምፕ



17.ፔትር ቼክ




16.ሙሐመድ ሳላህ



15.ሰርጂዮ አጉዌሮ



14.አሽሊ ኮል



13.ሪዮ ፈርዲናንድ



12.ጆን ቴይሪ




11.ሪያን ጊግስ




10.ፓትሪክ ቬይራ




9.ሮይ ኪን



8.ስቴቨር ዤራርድ




7.ፖል ስኮልስ




6.ፍራንክ ላምፓርድ




5.ኤሪክ ካንቶና




4.ዌይን ሩኒ




3.አሌን ሽረር





2.ክርስቲያኖ ሮናልዶ





1.ቴይሪ ሄንሪ



ምንጭ - Four Four Two

Thursday, February 27, 2020

የዕለተ አርብ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች

                            አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)



የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ ሌጀንድ ፖል ስኮልስ ቀያይ ሰይጣኖቹ ብሩኖ ፈርናንዴዝን ማስፈረማቸው ትክክል እንደነበር ተናግሯል።ስኮልስ የብሩኖ መምጣት ማን ዩናይትድን ለመ'ታየት የሚያጓጓ አድርጎታል ሲልም አክሏል።ፖርቱጋላዊው አማካይ ቲያትር ኦፍ ድሪምስ ከከተመ አንስቶ ሸጋ ጊዜን በማሳለፍ ላይ ይገኛል።
(Goal)





የቼልሲው አሰልጣኝ ፍራንክ ላምፓርድ ስምንት ተጨዋቾችን ከክለቡ ማሰናበት ይሻል።ኬፓ አሪዛባልጋ ፣ ጆርጊንሆ እና ሮዝ ባርክሌይ ደሞ ከተጨዋቾቹ ዝርዝር ውስጥ የሚገኙ ናቸው ሲል ሰን አስነብቧል።
(Sun)





ማንቸስተር ዩናይትድ ከሶስት አመታት በፊት 2017 ላይ የባየርን ሙኒኩን ካናዳዊ የግራ መስመር ተከላካይ አልፎንሶ ዳቪስ በ£2ሚ. የማዘዋወር ዕድል ገጥሞት ነበር።
(Times, subscription required)





የጅማት ጉዳት አጋጥሞት እስከ አመቱ መጨረሻ ከሜዳ እንደሚርቅ ሲነገርለት የነበረው እንግሊዛዊው የቶተንሃም አጥቂ ሀሪ ኬን ከታቀደው ቀደም ብሎ ሚያዚያ ወር ላይ ወደ ሜዳ ይመለሳል።
(Sun)





የአርሰናሉ ፈረንሳዊ አጥቂ አሌክሳንደር ላካዜት የ18 አመቱ የቡድን አጋሩ ቡካዮ ሳካን የወቅቱ ምርጡ ወጣት ተጨዋች ሲል ገልጾታል።እንግሊዛዊው የግራ መስመር ተከላካይ ሸጋ ጊዜን በመድፈኞቹ ቤት በማሳለፍ ላይ ይገኛል።
(Evening Standard)




በባየርን ሙኒክ አሳማኝ በሆነ መልኩ በሜዳው የተረታው ቼልሲ የክረምቱ የውድድር መስኮት አዳዲስ ተጨዋቾችን ለማዘዋወር ይሰራል።ሀኪም ዚያችን ከወዲሁ ማግኘቱን ያረጋገጠው ላምፓርድ ቀጣዩ እቅዱ የሊዮኑን ሀውሴም አውራ ማዘዋወር ነው።
(Tuttomercato)





ማንቸስተር ሲቲ የተከላካይ መስመሩን ለማጠናከር የኤቨርተኑን ሜሰን ሆልጌት የማዘዋወር ዕቅድ አለው።ፔፕ ጋርዲዮላ ከኤምሪክ ላፖርቴ ጋር የሚያጣምረውን ሁነኛ ተከላካይ በማሰስ ላይ ነው።
(The Mirror)




ማንቸስተር ሲቲ የፋይናንስ ጨዋነት ደንብን በመተላለፉ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የነጥብ ቅነሳ ቅጣት ሊደረግበት እንደሚችል እየተዘገበ ነው።ሲቲ በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ለሁለት ተከታታይ አመታት በሻምፒዮንስ ሊግ እንዳይካፈል መቀጣቱ ይታወሳል።
(Mail)





ሊቨርፑል ለኔዘርላንዳዊው የ28 አመት ተከላካይ ቨርጅል ቫን ዳይክ የዓለማችን ውዱ ተከላካይ ተከፋይ የሚያደርገውን አዲስ ኮንትራት ሊያቀርብለት ነው።
(Mirror)

Friday, February 21, 2020

የዕለተ አርብ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

በሰኞ የብሪጅ ጨዋታ ላይ ከእረፍት በፊት ተቀይሮ ከሜዳ የወጣው የቸልሲው ኒጎሎ ካንቴ በጉዳት ምክንያት ከ3-4 ሳምንታት ከሜዳ እንደሚርቅ ላምፓርድ ይፋ አድርጓል።




ጁቬንቱሶች ፖግባን ለማዘዋወር አዲስ የዝውውር ፓኬጅ ለዩናይትድ አዘጋጅተዋል።ጁቬዎች £50+ራምሴን በመስጠት ፖግባን ለመውሰድ ይፈልጋሉ።




በበርካታ የአውሮፓ ክለቦች እይታ ውስጥ የገባው የሬይኑ ወጣት አማካይ ኤዱዋርዶን ለማስፈረም የዚዳኑ ማድሪድ ክትትል ጀምረዋል።




የጣሊያኖቹ ጁቬዎች እና ኢንተር ሚላኖች የቸልሲውን ጣሊያናዊ የግራ መስመር ተጨዋች ኤመርሰን ፓልሚየርሚን ለማስፈረም ይፈልጋሉ።





ኢንተሮች የተከላካይ ክፍላቸውን ለማጠናከር የቬሮናውን ተከላካይ ማራሽ ኩምቡላ ለማስፈረም ፍላጎት አለው ፥ ሊቨርፑሎችም ተከላካዩን ይፈልጉታል።




ማንችስተር ሲቲ እና ባርሴሎና የኢንተር ሚላኑን ተከላካይ ሚላን ስክሪኒየር ማዘዋወር ከፈለጉ ኢንተሮች እስከ 90ሚዩ መክፈል እንደሚኖርባቸው ነግረዋቸዋል።




የሊቨርፑሉ ጆርዳን ሄንደርሰንን ለቀጣይ ሶስት ሳምንታት ከሜዳ እንደሚርቅ ተረጋግጧል።




ዩናይትድ ወሳኝ ተጨዋቾችን ከጉዳት መልስ አግኝቷል።ማክቶሚናይ እና ቱአንዛቤ ወደ ሙሉ ልምምድ ተመልሰዋል ማክቶሚናይ ለእሁዱ ጨዋታ ዝግጁ ነው በተጨማሪም ፖግባ ወደ ልምምድ ተመልሷል።

Thursday, February 20, 2020

የዕለተ አርብ ማለዳ ስፖርታዊ ዜናዎች

ትናንት ምሽት በዩሮፓ ሊግ በርካታ ጨዋታዎች የተደረጉ ሲሆን አርሰናል እና ኢንተር ሚላን ሲያሸንፉ ማንቸስተር ዩናይትድ አቻ ወጥቷል።



ሙሳ ዴንቤሌ ከቸልሲ ይልቅ ዩናይትድን መምረጡ ተሰምቷል።ፈረንሳዊው የሊዮን አጥቂ በክረምቱ ዩናይትድን እንደሚቀላቀል ይጠበቃል።




ኢንተር ሚላኖች በዚህ አመት ኮንትራቱ የሚጠናቀቀውን እና እስካሁን በናፖሊ አዲስ ኮንትራት ያልፈረመውን ድረስ መርተንስን በክረምቱ በነፃ ለማስፈረም እንቅስቃሴ ጀምረዋል።




በትላልቅ የአውሮፓ ክለቦች አይን ውስጥ የገባው የባየርን ሌቨርኩሰኑ ካይ ሀቬርትዝ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ወደ ትልቅ ክለብ ሊያመራ እንደሚችል የክለቡ ሀላፊዎች ፍንጭ ሰተዋል።





አርሰናሎች ለ24  አመቱ ጀርመናዊ ተከላካይ 40ሚ.ዩሮ ለመክፈል ፍላጎት አላቸው።በባየርን ሌቨርኩሰን ድንቅነቱን እያሳየ የሚገኘው ጆናታን ታህ በተለያዩ ክለቦች ቢፈለግም ማረፊያው ግን ኢምሬትስ ሊሆን እንደሚችል በሰፊው እየተነገረ ነው።





ጁቬንቱሶች በቀጣይ ክረምት የአጥቂ መስመራቸውን ለማጠናከር ፍላጎት አላቸው። እንደ ቱቶ ስፖርት ዘገባ ጁቬዎች ፊት መስመራቸውን ለማጠናከር ብራዚላዊውን የማን.ሲቲ አጥቂ ገብርኤል ጂሰስ እና በፒኤስጂ በውሰት የሚገኘውን ማውሮ ኢካርዲን ማስፈረም ይፈልጋሉ።




ዩናይትዶች ጄደን ሳንቾን እንደሚያስፈርሙት ተማምነዋል ነገር ግን ዩናይትዶች ሳንቾን ለማግኘት የግድ ቀጣይ አመት ቻምፒየንስ መሳተፍ የግድ ይላቸዋል።




አርሰናሎች የቀድሞ ኮከባቸውን ሳንቲ ካዞርላን ለማምጣት እና ተጫውቶ ደጋፊውን እንዲሰናበት ለማድረግ እያጤኑበት ይገኛል።ከዚህም በተጨማሪ ለካዞሮላ በአርሰናል ቤት አዲስ ሚና ሊሠጡት ፍላጎት አላቸው።

Wednesday, February 19, 2020

የዕለተ ረቡዕ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

ሌስተር ሲቲዎች በክረምቱ ከኮንትራት ነፃ የሚሆነውን የሊቨርፑሉን አዳም ላላናን በነፃ ለማስፈረም ድርድር መጀመራቸው ይፋ ተደርጓል።




በቶተንሀሙ ጨዋታ ላይ ጉዳት ደርሶበት ጨዋታውን ሳይጨርስ ከሜዳ ተቀይሮ የወጣው የማንችስተር ሲቲው ራሂም ስተርሊንግ ከጉዳቱ በማገገም ልምምድ ጀምሯል። ለሲቲዎችም መልካም ዜና ተብሏል። ሲቲ በቀጣይ ሳምንት በቻምፒየንስ ሊግ ማድሪድን ሲገጥም የስተርሊንግን ግልጋሎት ያገኛል።




አርሰናሎች የ18 ወራት ኮንትራት ብቻ በአርሰናል የሚቀረውን ወጣቱን ተጨዋች ባካዮ ሳካ የተሻለ ኮንትራት በማቅረብ በኢምሬት ለማቆየት ፍላጎት አላቸው። ተጨዋቹ በዩናይትድ ቸልሲ ባየርን ሙኒክ ይፈለጋል።





ላዚዮዎች በቸልሲ የመሰለፍ እድል የተነፈገውን እና በዚህ አመት መጨረሻ ኮንትራቱ የሚጠናቀቀውን ኦሊቨር ዡሩድን ለማስፈረም ኮንትራት አቅርበውለታል።




ባርሳዎች £18m በማውጣት የሌጋኔሱን አጥቂ ማርቲን ብሬዝዌይትን ዝውውር ለማዘዋወር ከጫፍ ደርሷል። ዝውውሩን በቀናት ውስጥ እንደሚጨርሱት ተነግሯል።





የአር ቢ ሌብዢኩ ፈረንሳዊው ተከላካይ ዳዮት ኦፓሜካኖ በተለያዩ ክለቦች ራዳር ውስጥ ገብቷል። በጥሩ የዝውውር መስኮት አርሰናልን ይቀላቀላል ሲባል ቢቆይም አሁን ላይ ተጨዋቹ ባርሴሎና እና ባየርንሙኒክ ጭምር ይፈለጋል።





በቀጣይ ዩናይትድ የሚሸጥ ከሆነ አዲሶቹ ባለቤቶች ለስታድየም እድሳት እስከ 200ሚ.ፓ ሊያወጡ እንደሚችሉ ተዘግቧል። እንደ ዘገባው ከሆነ በስታድየሙ የተለያዩ የፍሳሽ ማሶገጃዎች ችግር እንዳለባቸውና አይጦችም በብዛት እንደሚገኙ ተገልጿል።

Tuesday, February 18, 2020

የዕለተ ረቡዕ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች



ትናንት በሻምፒዮንስ ሊግ በተደረገ ጨዋታ ቦሩሲያ ዶርትመንድ ፔዤ ሲረታ ኤርሊንግ ሀላንድ የማሸነፊያዎቹን ሁለቱንም ግቦች አስቆጥሯል።ኖርዌጅያኑ አጥቂ ለጀርመኑ ክለብ በሰባት ጨዋታዎች 11 ግቦችን ነው ከመረብ ያሳረፈው።



ሪያል ማድሪዶች በጥር የዝውውር መስኮት ያስፈረሙትን ሬነርን ትናንት ከሰአት በይፋ አስተዋውቀውታል። ሬነር በራዎል በሚሰወጥነው ሁለተኛ ቡድን ካስቴላን እንደሚቀላቀል ይጠበቃል።




ሰንሁንግ ሚን በጉዳት ምክንያት በቀጣይ ሳምንታት የጆዜን ቡድን አያገለግልም።ከሀሪ ኬን ጉዳት ቡሀላም ለጆዜ ወሳኝ የሚባል ግልጋሎትን እየሰጠ የሚገኘው ሚን ቶተንሀም በቀጣይ በቻምፒየንስ ሊግ ደርሶ መልስ እንዲሁም በፕሪሚየር ሊጉ ከቸልሲ፣ ወልቭስ እና ዩናይትድ የሚያደርጉት ጨዋታዎች ያመልጡታል።




ዚያችን ለቸልሲ አሳልፈው የሰጡት አያክሶች ትላልቅ ተጨዋቾቻቸው ከትልልቅ የአውሮፓ ክለቦች ጋር ስማቸው እየተነሳ ይገኛል። በክረምቱም ብዛት ሊለቁባቸው ይችላሉ። በክረምቱ አያክስን ይለቃሉ ከተባሉት ውስጥ ዶኒ ቫንድቢክ በዩናይትድ እና ማድሪድ ግብ ጠባቂው ኦናና በቸልሲ ዳኒ ብሊንድ በአርሰናል  ቬልትማን፣ ታግሊያፊኮ እና ኔሬስ በተለያዩ ክለቦች የዝውውር ራዳር ውስጥ ገብተዋል።





የቀድሞ የባርሴሎና የማን.ሲቲ እንዲሁም የኦሎምፒያኮስ ተጨዋች ኮትዲቫራዊው ያያ ቱሬ በዚህ ሳምንት ወደ አንድ ክለብ ሊቀላቀል መሆኑ ተሰምቷል።ቱሬ በሳምንቱ መጨረሻ የብራዚሉን ክለብ ቦታፎጎ እንደሚቀላቀል ተሰምቷል።




ኤቨርተን እና ቶተንሀም በሮማ በውሰት ድንቅ አመትን በግሉ እያሳለፈ የሚገኘውን ንብረትነቱ የማንችስተር ዩናይትድ የሆነውን ክሪስ ስሞሊንግ ለማስፈረም ይፈልጋሉ።




ትናንት የዴምቤሌን መጎዳት ተከትሎ ሌላ ተጨዋች ለማስፈረም ጥያቄ አቅርበው ተቀባይነት ያገኙት ባርሴሎናዎች £17m የውል ማፍረሻ ያለውን የ28 አመቱን ማርቲን ብሬይዝዋይትን ለማስፈረም ፍላጎት አሳይተዋል።




የዩናይትድ ባለቤቶች የሆኑት የግሌዘር ቤተሰቦች ክለቡን የሚሸጡት 1ቢሊዮን ፓውንድ ከቀረበላቸው ብቻ መሆኑን አሳውቀዋል።

Monday, February 17, 2020

የዕለተ ሰኞ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

በሪያል ማድሪድ በጥብቅ እየተፈለገ የሚገኘው ራሂም ስተርሊንግ ትኩረቱ ለማንችስተር ሲቲ ብቻ እንደሆነ ተናገረ ።




የቀድሞ ጣሊያናዊ ኮከብ ዴል ፔሮ ፔፕ ጋርዲዮላ ትክክለኛው ለጁቬንቱስ የሚሆን አሰልጣኝ እንደሆነ ተናግሯል። የሲቲን ቅጣት ተከትሎ ፔፕ ከኢትሀድ መልቀቁ አይቀሬ ነው።





ማንችስተር ሲቲዎች አርብ ምሽት ለሁለት አመት ከአውሮፓ ውድድሮች መታገዱ ይታወሳል ፥  እናም ሲቲዎች ውሳኔውን ለማስቀየር ለይግባኝ ሰሚው አካል አቤቱታ አቅርበዋል።





የኦስማን ዴምቤሌን ጉዳት ተከትሎ ባርሴሎናዎች በላሊጋው አወዳዳሪ አካል በመጪው 15 ቀናት ውስጥ ተጨዋች እንያዘዋውሩ ፍቃድ አግኝተዋል።




በኖርዊች ጥሩ የሚባል አመትን እያሳለፈ የሚገጀው ካንትዌል በሌላኛው የእንግሊዝ ክለብ ሊቨርፑል ራዳር ውስጥ ገብቷል።ኖርዊቾች ከተጨዋቹ እስከ £30m ይፈልጋሉ።




ባርሴሎናዎች የወሳኝ ተጨዋቻቸውን ግልጋሎት ለሶስት ሳምንታት እንደማያገኙ ተሰምቷል። በላሊጋው ቅዳሜ እለት ተጎድቶ ከሜዳ የወጣው ጆርዲ አልባ ባርሴሎና በቀጣይ ሳምንት በቻምፒየንስ ሊግ እና በኤልክላሲኮ የአልባን ግልጋሎት አያገኝም።





በቅዳሜው ምሸት ጨዋታ ከስብስብ ውጭ ተደርገው የነበሩት ክሊያን ምባፔ እና ኔይማር ፒኤስጂ ዶርትመንድን ለመግጠም ከሚያመራው ስብስብ ውስጥ ተካተዋል።





ጀምስ ማዲሰን ዩናይትድን መቀላቀል ይፈልጋል። እንደሱ ፍላጎት ብቻ ቢሆን ኖሮ ከአመት በፊት ዩናይትድን ሊቀላቀል ይችል ነበር ተብሏል።

Sunday, February 16, 2020

የዕለተ ሰኞ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች

                          አቅራቢ- አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)



ምንም እንኳን ማንቸስተር ሲቲ ለተከታታይ ሁለት አመታት በሻምፒዮንስ ሊግ እንዳይሳተፍ ቢታገድም ፔፕ ጋርዲዮላ ግን በክለቡ ይቆያል።
(Mirror)





የቀድሞው የጁቬንትስ ሌጀንድ አሌሀንድሮ ዴልፔይሮ ፔፕ ጋርዲዮላ አሮጊቷን ቢይዝ ደስተኛ እንደሚሆን ተናግሯል።ፔፕ ማውሩዚዮ ሳሪን ተክቶ ቱሪን ሊከትም እንደሚችል በስፋት እየተነገረ ነው።
(Sky Sports)





የእንግሊዛዊው ራሂም ስተርሊንግ ወኪል ደንበኛው በክለቡ ላይ ሙሉ ትኩረቱን እንደሚያደርግ እና ስሙ ከዝውውር ጋር በስፋት በመነሳቱ እንደማይረበሽ ተናግሯል።
(Mirror)





ኦሌ ጉናር ሶልሻየር ማንቸስተር ዩናይትድ ለቀጣዩ አመት በሻምፒዮንስ ሊግ ሊያሳትፈው የሚችለውን ውጤት ባያስመዘግብም ክረምት ላይ ያለውን የዝውውር ዕቅድ እንደማይቀይረው ያስባል።
(Mirror)





ሶልሻየር ከቻይናው ክለብ ሻንጋይ ሺኖዋ በውሰት ማንቸስተር ዩናይትድን የተቀላቀለው ናይጄሪያዊው አጥቂ ኦዲዮን ኤግሃሎ በቋሚነት ኦልድ ትራፎርድ ሊቀር እንደሚችል ተናግሯል።
(Manchester Evening News)





ባርሴሎና የኢንተር ሚላኑን አርጀንቲናዊ አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ ከገንዘብ በተጨማሪ አንቱዋን ግሬዝማንን ለዝውውሩ አካል ሊያደርግ ይችላል።የላውታሮ ማርቲኔዝ የዝውውር ሂሳብ £92ሚ. ገደማ ነው።
(Sun)





ማንቸስተር ሲቲ በሻምፒዮንስ ሊግ የተጣለበት ዕገዳ የሚጸና ከሆነ በርካታ ወሳኝ ተጨዋቾቹን ሊያጣ እንደሚችል ይጠበቃል።
(Telegraph)






አር ቢ ሌብዚኽ ጀርመናዊውን አጥቂ ቲሞ ዋርነር ለማዘዋወር ሊቨርፑል ምንም አይነት ንግግር በቀጥታ ከነሱ ጋር እንዳላደረገ ተናግረዋል።ዋርነር በዚህ አመት 20 ግቦችን ማስቆጠር ችሏል።
(Mirror)






የዕለተ እሁድ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

አቅራቢ - ኢብራሒም ሙሐመድ




አሮጊቶቹ ፖግባን በክረምቱ ወደ ቱሪን ለመመለስ ትልቅ ፍላጎት አሳይተዋል።ከአውሮፓ ዋንጫ በፊት የፖግባን ዝውውር ለመጨረስ ራቢዮትን እና ራምሴን የዝውውሩ አካል ለማድረግ ፍላጎት አላቸው።




የፈረንሳይ ሚዲያዎች ከሰአት በሰበር ዜና መልክ ስለ ዳጆን ሳንቾ አዲስ ዜና ይዘው ወተዋል። ሳንቾ በተለያዩ ክለቦች ቢፈለግም ቸልሲዎች ተጨዋቹን ለማዘዋወር ከዶርትመንድ ጋር ንግግር ጀምረዋል።




ዩናይትዶች ሶልሻየርን ሚያሰናብቱት ከሆነ የቀድሞ የጁቬንቱስ አለቃ ማክሲሚሊያኖ አሌግሪን ለመቅጠር ፍላጎት እንዳላቸው ተሰምቷል።አሌግሪ ከዩናይትድ በተጨማሪ የፈረንሳዩ ሀያል ክለብ ፒኤስጂም ይፈልገዋል።





የሌስተር ሲቲው አሰልጣኝ ብሬንዳን ሮጀርስ ከቀድሞ ልጁ ጋር ለመገናኘት ፍላጎት አሳይተዋል።ሮጀርስ ፊቱን ወደ አርሰናሉ ግራ መስመር  ተከላካይ ኬራን ቴርኒ ላይ አርገዋል። እንደ ምክንያት የተነሳው ደሞ ሌስተሮች ቤን ቺልዌልን በክረምቱ ማጣታቸው አይቀሬ ስለሆነ ነው።





ሊቨርፑሎች ጀርመናዊውን የአርቢ ሌብዢኩን አጥቂ ቲሞ ዋርነር ለማስፈረም ከሌብዢክ ጋር ድርድር መጀመሩ ተሰምቷል።ሊቨርፑሎች ለተጨዋቹ እስከ £50m ለመክፈል ፍቃደኛ ናቸው።




ኢንተር ሚላኖች ላውታሮ ማርቲኔዝን ለባርሴሎና የሚሸጡ ከሆነ በምትኩ አንቱዋን ግሪዝማንን ይፈልጋሉ።





ወደ ዩናይትድ ይገባል ሲባል የቆየው ማውሪዚዮ ፖቸቲንሆ ሳይታሰብ ቀጣይ ማረፊያው እዛው ማንችስተር ከተማ ማን.ሲቲ ሊሆን ይችላል።እንደ መረጃዎች ከሆነ ፔፕ ሲቲ ለሁለት አመት ከአውሮፓ ውድድሮች መታገዱን ተከትሎ በኢትሀድ የመቆየት እድሉ ጠባብ ነው።

Saturday, February 15, 2020

የዕለተ ቅዳሜ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

              አቅራቢ - ኢብራሒም ሙሐመድ


የዩናይትድ ባለ ስልጣኖች ፖል ፖግባን በመልቀቅ በምትኩ የሌስተሩን ጀምስ ማዲሰን እና የአስቶንቪላውን ጃክ ግሪሊሽን ለማስፈረም እንደሚፈልጉ ታውቋል።




አርሰናሎች ለፔር ኤምሪክ ኦባምያንግ የመሸጫ ሂሳብ አውተውለታል።አርሰናሎች ማንኛውም £70m ይዞ ለሚመጣ ክለብ የ30 አመቱን ኮከብ ለመልቀቅ ፍቃደኛ ናቸው።





ሊቨርፑሎች ሮበርት ፈርሚንሆን ሚያጡ ከሆነ በሱ ምትክ የቤኔፊካውን አጥቂ ካርለስ ቪኒሲየስት ለማስፈረም ይፈልጋሉ።ተጨዋቹ በቤኔፊካ ውል ማፍረሻው £100m ሲሆን ሊቨርፑሎች ግን £50m በመክፈል እንደሚወስዱ ተማምነዋል።




ዚነዲን ዚዳን ለሶስት ወራት ከሜዳ እርቆ የቆየው ኤደን ሀዛርድ ነገ በበርናባው ማድሪድ ሴልታቪጎን ሲገጥም ወደ ሜዳ እንደሚመለስ አረጋግጧል።





እንደ ላጋዜታዴሎ ስፖርት ዘገባ ከሆነ ጁቬንቱሶች በዚህ አመት መጨረሻ ውሉ የሚጠናቀቀውን ፈረንሳዊው አማካይ ብለስ ማቲዩዲን ውል ለማራዘም ድርድር መጀመሩ ታውቋል።





ምባፔ እና ኔይማር ፒኤስጂ ዛሬ ምሽት ከአሚነስ ጋር ከሚያደርገው ጨዋታ ስብስብ ውጪ ሆነዋል። ምክንያቱ ደግሞ ፒኤስጂ ከቀናት ቡሀላ ከዶርትመንድ ጋር ለሚያደርገው የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ መሆኑ ታውቋል።





ቸልሲ እና አርሰናል አይናቸውን ስፔናዊው ኮከብ ላይ ኢስኮ አልካሴር ላይ ጥለዋል። ማድሪዶች ለኢስኮ እስከ £65m ይፈልጋሉ።ተጨዋቹ በክረምት መልቀቁ አይቀሬ ነው።

Friday, February 14, 2020

የዕለተ ቅዳሜ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች

                   አቅራቢ- አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)


አርሰናል እና ቼልሲ ስፔናዊውን የሪያል ማድሪድ አማካይ ኢስኮ በ£63ሚ. ለማዘዋወር ፉክክር ውስጥ ገብተዋል።ሪያል ማድሪድ በክረምት ታላላቅ ዝውውሮችን የመፈጸም ዕቅድ ስላለው ከወዲሁ ኢስኮ የመሸጥ ፍላጎት አለው።
(Sun)





ትናንት ማንቸስተር ሲቲን ከአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለሁለት ተከታታይ አመታት ማገዱን የአውሮፓ እግር ኳስ ማሐበር ይፋ አድርጓል።የUEFAን የተለያዩ ህጎች የጣሰው ሲቲ £30ሚ. የገንዘብ ቅጣትም ተጥሎበታል።
(Mirror)





ያለ አግባብ ተጨዋቾችን በማስፈረሙ ከሻምፒዮንስ ሊግ ለሁለት አመት የታገደው ማንቸስተር ሲቲ በእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበርም ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችል እየተነገረ ነው።ቅጣቱም በሊጉ ላይ የነጥብ ቅነሳ እንደሚሆን ተጠቁሟል።
(Star)





ፖል ፖግባ ክረምት ላይ ከማንቸስተር ዩናይትድ የመውጣት ፍላጎት አለው።ሆኖም ማንቸስተር ዩናይትድ ለዝውውሩ ከፈላጊ ክለቦች የጠየቀው የተጋነነ ሒሳብ ህልሙን እንዳያሳካ ሳንካ ሊሆንበት ይችላል።
(Guardian)





ኢንተር ሚላን አርጀንቲናዊውን አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ የሚያጣ ከሆነ የአርሰናሉን ጋቦናዊ አጥቂ ፔር ኤምሪክ ኦባማያንግ ማዘዋወር ይፈልጋል።
(Star)




ማንቸስተር ዩናይትድ ፈረንሳዊውን የሊዮን አጥቂ ሙሳ ዴምቤሌ ለማዘዋወር £60ሚ. አሰናድቷል።ኦሌ ጉናር ሶልሻየር የ23 አመቱን ተጨዋች አጥብቆ ይሻዋል።
(Star)





ቶተንሃም የኖርዊች ሲቲውን ተከላካይ ቤን ጎድፍሬይ ለማዘዋወር ፍላጎት አለው።የ22 አመቱ እንግሊዛዊ የዝውውር ሒሳቡ £50ሚ. ገደማ ነው።
(Express)





ፓሪሰን ዤርመን በተለይ በሪያል ማድሪድ በጥብቅ የሚፈለገውን ፈረንሳዊውን አጥቂ ኪሊያን ምባፔ በፓርክ ደ ፕሪንስ ለማቆየት አዲስ ኮንትራት ሊያቀርብለት ነው።እንደ ሚረር ዘገባ ከሆነ አዲሱ ኮንትራት ለ21 አመቱ አጥቂ በአመት £41ሚ. ያስገኝለታል።
(Mirror)

የዕለተ አርብ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

                       አቅራቢ - ኢብራሒም ሙሐመድ



የአውሮፓ ታላላቆቹ ክለቦች ሪያል ማድሪድ እና ሊቨርፑል የኢንተር ሚላኑን አማካይ ማርሴሎ ብሮዞቪችን ለማስፈረም ፉክክር ውስጥ ገብተዋል።





የቱርኩ ቤሺክታሽ ግብፃዊውን መሀመድ ኤኔኒን በክረምቱ የዝውውር መስኮት ከአርሰናል በውሰት ማስፈረማቸው ይታወሳል ፥ እናም ቤሺክታሾች ዝውውሩን ቋሚ ለማድረግ ከአርሰናል ጋር ንግግር ለማድረግ ዝግጁ ናቸው።




ኢንተርሚላኖች ሆላንዳዊውን የዩናይትድ ወጣት ተጨዋች ታሂት ቾንግን ለማስፈረም ከጫፍ ደርሰዋል። ወጣቱ ቾንግ በዚህ አመት መጨረሻ ኮንትራቱ የሚጠናቀቅ ይሆናል። በዚህም ኢንተሮች ልጁን በነፃ ያገኙታል።





ፒኤስጂዎች ወጣቱን ግብ ጠባቂ ዲን ሄንደርሰንን ከዩናይትድ ለማስፈረም ፍላጎት አላቸው። በአሁን ሰአት ሄንደርሰን ለሼፍልድ በውሰት እየተጫወተ ይገኛል። ከፒኤስጂ  በተጨማሪም ቸልሲ፣ቶተንሀም እና በውሰት ሚጫወትበት ሼፍልድ የልጁ ፈላጊ ናቸው።




በዩናይትድ በጥብቅ ሚፈለገው እንግሊዛዊው የአስቶንቪላ ተጨዋች ጃክ ግሪሊሽ በክረምቱ ወደ ዩናይትድ ማምራት እንደሚፈልግ ለክለብ ጉዋደኞቹ ነግሮዋቸዋል።




አርሰናሎች በክረምቱ ባየርን ሙኒክን መልቀቁ እውን ለመሆን የተቃረበውን ፈረንሳዊውን ኮረንቲን ቶሊሶን በክረምቱ የዝውውር መስኮት ሊያስፈርሙት ይፈልጋሉ።





ሪያል ማድሪዶች በተለያዩ ክለቦች የሚፈለገውን የኢንተር ሚላን አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝን ለማስፈረም እንቅስቃሴ ጀመሩ።ኢንተሮች ተጨዋቹን የመሸጥ ፍላጎት የላቸውም።

Thursday, February 13, 2020

የዕለተ አርብ ስፖርታዊ ዜናዎች

                አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)


ማንቸስተር ዩናይትድ ፈረንሳዊውን የሊዮን አጥቂ ሙሳ ዴምቤሌ ለማዘዋወር £60ሚ. አሰናድቷል።ኦሌ ጉናር ሶልሻየር የ23 አመቱን ተጨዋች አጥብቆ ይሻዋል።
(Star)





ቶተንሃም የኖርዊች ሲቲውን ተከላካይ ቤን ጎድፍሬይ ለማዘዋወር ፍላጎት አለው።የ22 አመቱ እንግሊዛዊ የዝውውር ሒሳቡ £50ሚ. ገደማ ነው።
(Express)





ፓሪሰን ዤርመን በተለይ በሪያል ማድሪድ በጥብቅ የሚፈለገውን ፈረንሳዊውን አጥቂ ኪሊያን ምባፔ በፓርክ ደ ፕሪንስ ለማቆየት አዲስ ኮንትራት ሊያቀርብለት ነው።እንደ ሚረር ዘገባ ከሆነ አዲሱ ኮንትራት ለ21 አመቱ አጥቂ በአመት £41ሚ. ያስገኝለታል።
(Mirror)





በሻምፒዮንስ ሊግ በደርሶ መልስ በሪያል ማድሪድ የሚሸነፍ ከሆነ ማንቸስተር ሲቲ ሊያሰናብተው እንደሚችል ፔፕ ጋርዲዮላ ተናግሯል።ማን ሲቲ በዘንድሮው አመት ከወትሮው በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊጉም ደካማ ጊዜን በማሳለፍ ላይ ይገኛል።
(Guardian)




ሪያል ማድሪድ አርጀንቲናዊውን አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ ከኢንተር ሚላን ለማዘዋወር የውል ማፍረሻውን €120ሚ. ለመክፈል ዝግጁ ነው።የ22 አመቱ ተጨዋች በዘንድሮው አመት እያሳየ ባለው ድንቅ አቋም በበርካታ ጉምቱ የአውሮፓ ክለቦች አይን ውስጥ ገብቷል።
(TyC Sports)





ሜሲ በባርሴሎና ደስተኛ መሆኑን የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኙ ስካሎኒ ተናገረ።ሰሞኑን ሜሲ ከባርሴሎና ሊለቅ እንደሚችል በስፋት ሲዘገብ መቆየቱ ይታወሳል።
(Goal)





በባርሴሎና ያለው ቆይታ ጥያቄ ምልክት ውስጥ የገባው ኢቫን ራኪቲች በጁቬንትስ ከክርስቲያኖ ሮናልዶ ጋር ቢጫወት ደስተኛ እንደሚሆን ተናግሯል።ራኪቲች ከጁቬንትስ በተጨማሪ በኢንተር ሚላን ፣ በማንቸስተር ዩናይትድ እና ፓሪሰን ዤርመን ይፈለጋል።
(Goal)





ጁቬንትስ ብራዚላዊውን አጥቂ ዊልያን ከቼልሲ ለማዘዋወር ፍላጎት ቢኖረውም ዊልያን ግን ከማውሩዚዮ ሳሪ ጋር በዚህ ፍጥነት ዳግም መስራት አይሻም።
(Express)











የዕለተ ሐሙስ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

                     አቅራቢ- ኢብራሒም ሙሐመድ



ቶማስ ቱሄል ከትናንቱ ምሽት የፈረንሳይ ካፕ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ቡሀላ ስለ ኔማር ጉዳት ዜና አዲስ ነገር ይፋ አድርጓል። ኔማር ፒኤስጂ በቀጣይ ሳምንት ዶርትመንድን በቻምፒየንስ ሊጉ ሲገጥሙ  ለጨዋታው መድረስ እድሉ ጠባብ እንደሆነ ተናግሯል።




ዩናይትድ እና ሊቨርፑል የስታድየም ማስፋፊያ ሊያደርጉ ነው። ቀያይ ሰይጣኖቹ ተጨማሪ 1,500 ተመልካች የሚይዝ መቀመጫዎችን ለመስራት ሲያስቡ ሊቨርፑሎች ተጨማሪ 7,000 መቀመጫ ወንበሮችን ለመስራት አስበዋል።




በጉዳት ምክንያት ከዚህ አመት ውድድር ውጭ ነው ሲባል የሰነበተው የባርሴሎና አጥቂ ሉዊስ ሱዋሬዝ ከተባለለት ቀን በፊት ወደ ልምምድ ሊመለስ ይችላል። እንደ መረጃዎች ከሆነ ሱዋሬዝ በሚያዚያ ወር ውስጥ ልምምድ እንደሚጀምር ተሰምቷል።





ኤደን ሀዛርድ ከሶስት ወር ቆይታ ቡሀላ ወደ ሜዳ ሊመለስ ነው።ማድሪዶች እሁድ ከሴልታቪጎ ለሚያደርጉት ጨዋታ ዝግጁ ነው።እንዲሁም ከሲቲ ላለባቸው የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ዝግጁ ነው።





ቸልሲ ሀኪም ዚያችን ማስፈረሙን አረጋግጧል። ተጨዋቹ የቸልሲ ንብረት መሆኑን ቸልሲም አያክስም ይፋ አድርገዋል።ቸልሲ ለተጨዋቹ £40m ለአያክስ ሲከፍል የክረምቱ የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ሲከፈት ተጨዋቹ በይፋ የቸልሲ ንብረት ይሆናል።





አርሰናሎች ለማቲዮ ጉንዶዚን አዲስ ኮንትራት ሊያቀርቡለት ነው።ጉንዶዚን በአርሰናል ኮንትራት ቢኖረውም አርሰናሎች የወደፊቱን በማሰብ ተጨማሪ ኮንትራት ሊያቀርቡለት ነው።






ዳጀን ሳንቾ በክረምት ዶርትመንድን መልቀቁ እውን መሆኑን ስካይ ስፖርት አስነብቧል። ቀጣዩ ጥያቄ የተጨዋቹ ማረፊያ የት ነው ሚለው ነው፥ ተጨዋቹን ቸልሲ እና ዩናይትድ በጥብቅ ይፈጉታል። ነገር ግን ቸልሲዎች ዚያችን ስላገኙ ሳንቾን እንደተዉት እርግጥ ሆኗል።ስለሆነም የተጨዋቹ ቀጣይ ማረፊያ ዩናይትድ ሊሆን ይችላል።





የባርሴሎናው ፕሬዝዳንት ጆዜፕ ባርቶሚዮ በመጪው ክረምት ኔማርን ለማስፈረም ዝግጁ ሆነዋል።እንደ ካታላን ጋዜጦች ከሆነ ባርቶሚዮ ኔማርን ለማስፈረም ሁለት ትላልቅ ሚባሉ ተጨዋቾችን ለመሸጥ ዝግጁ ሆነዋል።

Wednesday, February 12, 2020

የዕለተ ሐሙስ ማለዳ ስፖርታዊ ዜናዎች

           አቅራቢ- ኢብራሒም ሙሐመድ


በክረምቱ ቡድናቸውን እንደ አዲስ ለመገንባት በሂደት ላይ የሚገኙት ባቫሪያኖቹ የተለያዩ ተጨዋቾችን ሊለቁ እንደሆነ ተሰምቷል። ባቫሪያኑ ሳይታሰብ ፈረንሳዊውን አማካይ ኮረንቲያን ቶሊሶን ለመሸጥ ፍላጎት አሳይተዋል።




ለፖርቶ የሚጫወተው ስፔናዊው የግብ ዘብ ኢከር ካሲያስ ለ2020 ለሚካሄደው የስፔን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምርጫ እንደሚወዳደር እራሱ ካሲያስ ይፋ አድርጓል።




ከቶተንሀም ከለቀቀ ቡሀላ እስካሁን ወደ አሰልጣኝነት ያልተመለሰው ማውሪዚዮ ፖቸቲንሆ ወደ ዩናይትድ ለመግባት ፍንጭ ሰቷል።ትናንት ምሽት በእንግሊዝ ሻምፒዮን ሺፕ ብሬንትፎርድስ ከ ሊድስ ያደረጉትን ጨዋታ ከአዲሱ የኢድ ውድዋርድ አማካሪ ከኒል አሽተን ጋር በቅርብ መቀመጫ ሆነው ታድመዋል።ከጨዋታው ቡሀላም ሲገናኙ የሚያሳይ ምስል ወቷል።





በተለያየ ጊዜ ለጉዳት ሚጋለጠው ፈረንሳዊው የባርሴሎና ተጨዋች ኡስማን ዴንቤሌ ቀዶ ጥገናውን በተሳካ ሁኔታ አከናውኗል። ባርሴናዎች ዴምቤሌ ለሚቀጥሉት 6 ወራት ከሜዳ እንደሚርቅ አረጋግጠዋል።




ቸልሲዎች መልሶ የመግዛት መብታቸውን ተጠቅመው ሆላንዳዊውን የበርንማውዝ የቀድሞ ልጃቸውን ናታት አኬን በ£40m ለማስፈረም ፍላጎት አላቸው።




አያክሶች በክረምቱ ከኮንትራት ነፃ የሚሆነውን የቀድሞ ልጃቸውን የቶተንሀሙን የ32 አመቱን ቤልጄማዊ ተከላካይ ያን ቬርቶጋትንን ለማስፈረም ፍላጎት አላቸው።




በክረምቱ ከኮንትራትነፃ የሚሆነው ድረስ መርተንስ በክረምቱ ወደ ፕሪሚየር ሊግ መዘዋወር እንደሚፈልግ ተሰምቷል። ዩናይትድ፣ አርሰናል እና ቸልሲ የልጁ ፈላጊ ናቸው።




ዩናይትዶች የዶርትመንዱንኮከብ ጃደን ሳንቾን ለማስፈረም ይፈልጋሉ።ዩናይትዶች ቸልሲን በልጠው ልጁን በ£120m ለማስፈረም እቅድ አላቸው።

"ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መመለስ እፈልጋለሁ" ፖቼቲንሆ

                አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)


"ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መመለስ እፈልጋለሁ" ፖቼቲንሆ



ከአምስት አመታት ቆይታ በኋላ በዚህ ሲዝን ከቶተንሃም ጋር የተለያየው እና አሁን አዲስ ክለብ ለመያዝ እየጠበቀ የሚገኘው አርጀንቲናዊው አሰልጣኝ ማውሩሲዮ ፖቼቲንሆ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መመለስ እንደሚሻ ለIn the pink ተናግሯል።


ስሙ በስፋት ከማንቸስተር ዩናይትድ ጋር በተጨማሪም ከሪያል ማድሪድ ፣ ጁቬንትስ እና ባየርን ሙኒክ ጋር  ሲያያዝ የቆየው የ47 አመቱ ሰው እንዲህ ነው ያለው:

"እውነቱን ለመናገር ፥ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዳግም ብሰራ እወዳለሁ።ከባድ እንደሚሆን እረዳለሁ።አሁን ግን ሰከን ብዬ የሚሆነው የምጠባበቅበት ጊዜ ላይ ነኝ።አሁን ስለ እራሴ የማስብበት የስክነት ጊዜ ላይ ነኝ።በተጨማሪም ለሚመጣው ነገር መሰናዳት ያስፈልጋል ምክንያቱም በእግር ኳስ ምን እንደሚፈጠር አይታወቅም።


"ለአዲስ ስራ ዝግጁ ሆኜ በመጠበቅ ላይ ነው የምገኘው።ቀጣዩ የስራ ዘመኔ አስደናቂ እንደሚሆን እተማመናለሁ።"

Tuesday, February 11, 2020

የዕለተ ረቡዕ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች

                  አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)


ማንቸስተር ዩናይትድ በቼልሲ በጥብቅ የሚፈለገውን እንግሊዛዊውን የቦሩሲያ ዶርትሙንድ አጥቂ ጄደን ሳንቾ ለማዘዋወር £120ሚ. አሰናድቷል።
(Mirror)





ሊቨርፑል ለኔዘርላንዳዊው ተከላካይ ቨርጅል ቫን ዳይክ አዲስ ኮንትራት ሊያቀርብለት ነው።በአዲሱ ኮንትራት መሰረት የ28 አመቱ ተከላካይ በሳምንት ከ£150,000 በላይ እንደሚከፈለውም ይጠበቃል።
(Football Insider)





ማንቸስተር ዩናይትድ በቀጣዩ ክረምት የሊዮኑን የ23 አመት ፈረንሳዊ አጥቂ ሙሳ ዴምቤሌ ለማዘዋወር ጥረት ያደርጋል።
(L'Equipe, via Manchester Evening News)




ቶተንሃም ሆላንዳዊውን የበርንማውዝ ተከላካይ ናታን አኬ ለማዘዋወር £40ሚ. አሰናድቷል።ጆዜ ሞሪንሆ የተከላካይ ስፍራቸውን ማጠናከር አጥብቀው ይሻሉ።
(Express)





ቤልጄሚያዊው የናፖሊ አጥቂ ድረስ መርቲንስ በአመቱ መጨረሻ በኔፕልስ ያለው ኮንትራት የሚያበቃ ሲሆን ቼልሲ ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና አርሰናል ደግሞ ፈላጊዎቹ ናቸው።
(Mail)





ቼልሲ በጥር ወሩ የዝውውር መስኮት ሁለት ጊዜ ሊያዘዋወር ሞክሮ ያልተሳካለትን የአያክሱን ሞሮኮዋዊ የክንፍ አጥቂ ሀኪም ዚያች  ለማዘዋወር አሁንም በመስራት ላይ ይገኛል።
(Telegraph)





ክረምት ላይ በቶተንሃም ያለው ኮንትራት የሚያበቃውን ቤልጄሚያዊውን ተከላካይ ያን ቨርቶገን ለማዘዋወር አያክስ ፍላጎት አለው።
(Guardian)





ማንቸስተር ሲቲ ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ፣ ሊቨርፑል እና አትሌቲኮ ማድሪድ የቬሮናውን አልባኒያዊ ተከላካይ ማራሽ ኩምቡላ ለማዘዋወር ፉክክር ውስጥ ገብተዋል።
(Gazzetta dello Sport, via Sport Witness)






የዕለተ ማክሰኞ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

                     አዘጋጅ- ኢብራሒም ሙሐመድ


ማንችስተር ሲቲዎች ኤርሊንግ ሀላንድን የሰርጂዮ አጉዌሮ የረጅም ጊዜ ተተኪ ለማድረግ ፍላጎት አላቸው። ሲቲዎች ለአጉዌሮ የወደፊቱ እጣ ፋንታው በእጁ ላይ እንዳለ ነግረውታል በኢትሀድ መቆየት ወይም ከኢትሀድ መልቀቅ።





በጥርየ ዝውውር መስኮት ወደ ኤሲ ሚላን ለማምራት ከጫፍ ደርሶ የነበረውን የዊጋን አትሌቲኩ የግራ መስመር ተጨዋች አንቶኒ ሮቢንሰን በሶስቱ የእንግሊዝ ክለቦች ቸልሲ፣ ኒውካስትል እና አስቶንቪላ የዝውውር ራዳር ውስጥ ገብቷል።




በተለያየ ጊዜ በትላልቅ ክለቦች ራዳር ውስጥ ሚገባው የዋትፎርዱ አብዱላሂ ዶኮሬ በቀጣይ አመት በቻምፒየንስ ሊግ ለሚጫወት ክለብ መጫወት እንደሚፈልግ ተናገረ። በክረምትም ዋትፎርዶች እንዲለቁት ጥያቄ አቅርቦላቸዋል።





ታላላቆቹ የእንግሊዝ ክለቦች ፖርቱጋላዊውን ተከላካይ ሩበን ዲያዝን ለማስፈረም ተፋጠዋል። በተለይም በተደጋጋሚ ስማቸው ከልጁ ጋር ሚነሳው ዩናይትዶች ባሳለፍነው ሳምንት መልማዮችን ልከው ልጁን መመልከታቸው ታውቋል። ከዩናይትድ በተጨማሪም ማን ሲቲ ቶተንሀም ሊቨርፑል የልጁ ዋና ፈላጊዎች ናቸው።





በማውሪዚዮ ሳሪ ደስተኛ ያልሆኑት ጁቬንቱሶች ኢላማቸውን ስፔናዊውን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላን አርገዋል። ጁቬዎች ጋርዲዮላን ዘንድሮ ባያገኙትም ሲቲን በሚለቅ ሰአት ለመቅጠር ዝግጁ ሆነዋል።




ቸልሲዎች ለሀርት ፑል የሚጫወተውን የ17 አመቱን ግብ ጠባቂ ብራድ ያንግን ለማስፈረም ከዩናይትድ እና ከአርሰናል የተሻለ እድል እንዳላቸው ተሰምቷል።





ዩሊያንት ብራንት በጉዳት ምክንያት ለአንድ ወር ቦሩሲያ ዶርትመንድን እንደማያገለግል ተረጋግጧል። በዚህም ዶርትመንዶች በቻምፒየንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ፒኤስጂን ሲገጥሙ በሁለቱም ጨዋታዎች የብራንትን ግልጋሎት አያገኙም።

Monday, February 10, 2020

የዕለተ ማክሰኞ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች

                አቅራቢ- አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)



ጁቬንትስ የማንቸስተር ሲቲውን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በዋና አሰልጣኝነት ለመሾም ፍላጎት አላት።አሮጊቷ ለ49 አመቱ ስፓኒያርድ ከፍተኛ ደሞዝ እና ጥሩ ፕሮጀክትም አሰናድታለታለች።
(Sun)





ባርሴሎና ብራዚላዊውን የ27 አመት አማካይ ፌሊፔ ኩቲንሆ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት እንደሚለቀው ይጠበቃል።ኩቲንሆ በማንቸስተር ዩናይትድ ፣ ቼልሲ ፣ ማንቸስተር ሲቲ ፣ ቶተንሃም እና በቀድሞው ክለቡ ሊቨርፑል ይፈለጋል።
(Express)





ማንቸስተር ሲቲ ኖርዌያዊውን የቦሩሲያ ዶርትሙንድ አጥቂ ኤርሊንግ ሀላንድ የረዥም ጊዜ የሰርጂዮ አጉዌሮ ተተኪ ማድረግ ይሻል።ሀላንድ በዚህ ሲዝን ድንቅ እንቅስቃሴን በማድረግ ብዙሃኑን የእግር ኳስ አፍቃሪ አጀብ ያሰኘ አጥቂ ነው።
(90min.com)





የቶተንሃሙ አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት የበርንማውዙን ተከላካይ ናታን አ'ኬ እና የቤኔፊካውን ተከላካይ ሩበን ዲያዝ ለማዘዋወር አቅደዋል።
(Express)





ማንቸስተር ዩናይትድ በውሰት ለኢንተር ሚላን የሰጠውን የ31 አመቱን ቺሊያዊ አጥቂ አሌክሲስ ሳንቼዝ ለመሸጥ ፍላጎት ያለው ሲሆን ገዢዎችን በማፈላለግ ላይ ይገኛል።
(Manchester Evening News)





የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ክለቡ አሁን እስከ አራተኛ ደረጃ ይዞ የማጠናቀቅ ዕድሉ አዳጋች ሊሆን እንደሚችል ተናግሯል።መድፈኞቹ አራተኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው የከተማ ተቀናቃኛቸው ቼልሲ በአስር ነጥብ ያንሳሉ።
(Evening Standard)





ማንቸስተር ዩናይትድ ለ2020-21 ቅድመ ዝግጅት አዲስ ዕቅድ ለማውጣት እየተሰናዳ ነው።የዚህ ምክንያት ደግሞ መጀመሪያ ዕቅዳቸው ቻይና ስለነበር እና አሁን በቻይና ኮሮና ቫይረስ በመከሰቱ ሳቢያ ነው ተብሏል።
(ESPN)






አሁን በኢንተር ሚላን የሚገኘው የቀድሞው የቶተንሃም አማካይ ክርስቲያን ኤሪክሰን በተጨዋችነት ህይወቱ እንደ ሚላን ደርቢ አይነት ድንቅ ድባብ አይቶ እንደማያውቅ ተናግሯል።
(Goal)





የዕለተ ሰኞ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

አዘጋጅ - ኢብራሒም ሙሐመድ



                            


ባየርን ሙኒኮች ፊሊፔ ኩቲትሆን እንዲሁም ሊዩሬ ሳኔን ማስፈረም ይፈልጋሉ።እንደ  ዘገባዎች ከሆነ ሙኒኮች ለኩቲንሆ እስከ £75m መድበዋል ሊቨርፑሎችም ከአሁኑ ስጋት ውስጥ ገብተዋል ።




በዚህሳምንት ጉዳት ላይ የነበሩት በጨዋቾች ወደ ልምምድ እየተመለሱ ይገኛሉ. ከጥር መጀመሪያ  ጀምሮ ለዩናይትድ ግልጋሎት ያልሰጠው ስኮት ማክቶሚናይ ወደ ልምምድ ተመልሷል። እንዲሁም የሊቨርፑሉ ሳዲዮ ማኔም ወደ ልምምድ ተመልሷል።




በበርካታ ታላላቅ የአውሮፓ ክለቦች የሚፈለገው ሴኔጋላዊው የናፖሊ ተከላካይ ካሊዱ ኩሊባሊ በክረምቱ ወደ ዩናይትድ የማምራት እድሉ ሰፊ ነው።




ጁቬዎቹ በክረምቱ ፖል ፖግባን ለማስፈረም ቀዳሚ ምርጫቸው አድርገውታል።እንደ ካልቺዮ መርካቶ ዘገባ ከሆነ ጁቬዎች በክረምቱ ትልልቅ ዝውውር ለመፈፀም ዝግጅት ላይ ሲሆኑ ተጨዋቹም ፖግባ ሆኗል።




ከጊዜወደጊዜ መሻሻሎችን እያሳየ የሪያል ማድሪዱ ቲቦቱ ኮርቱዋ የስፔን ላሊጋ የወሩ ምርጥ ተጨዋች ሆኗል።




ሊቨርፑሎች በክረምቱ የዝውውር መስኮት የመሀል አማካይ ለማስፈረም ፍላጎት አላቸው። ከአሁኑም ስማቸው ከተለያዩ ተጨዋቾች ጋር እየተነሳ ይገኛል። የክሎፕ ተቀዳሚ ምርጫ ግን የባየርን ሌቨርኩለኑ ካይ ሀቨርትስ ነው። በተጨማሪም ሊቨርፑሎች የቀድሞ ኮከባቸውን ከቲትሆንም መመለስ ይፈልጋሉ።




ካሜሮናዊው የአያክስ ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና የመጀመሪያ ምርጫው ቸልሲ ሆኗል።በተለያዩ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች ባርሴሎና እና ፒኤስጂ ቢፈለግም ተጨዋቹ ግን በላምፓርድ እምነት ያጣውን አሪዛባላጋን በመተካት ብሪጅ መድረስ ነው ሚፈልገው።



በዚህ ሳምንት የእንግሊዝ ክለቦች እረፍት መሆናቸው ይታወሳል።ይህንንም ተከትሎ ጆዜ ትናንት በአሊያንዝ አሬና በመገኘት የአርቢ ሌብዢክን ጨዋታ ተመልክተዋል።ቶተንሀሞች በቀጣይ ሳምንት በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ሌብዢክን ይገጥማል።

Sunday, February 9, 2020

የዕለተ ሰኞ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች

               አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)



ባየርን ሙኒክ ብራዚላዊውን የሊቨርፑል አጥቂ ሮበርቶ ፈርሚንሆ ለማዘዋወር £75ሚ. የመደበ ሲሆን የባቫሪያው ክለብ የማንቸስተር ሲቲውን ለሮይ ሳኔንም ማዘዋወር ይሻል።
(Sun)




በማንቸስተር ዩናይትድ የአንድ አመት ኮንትራት የቀረው ፈረንሳዊው ኢንተርናሽናል ፖል ፖግባ በመጪው ክረምት ከቲያትር ኦፍ ድሪምስ ለመውጣት አቅዷል።የ26 አመቱ ኮከብ በዚህ አመት በጉዳት ምክንያት በርካታ ጨዋታዎች ላይ አለመሰለፉ ይታወቃል።
(Manchester Evening News)





ማንቸስተር ዩናይትድ በጥብቅ ሲፈልገው የነበረው እንግሊዛዊው የሌስተር ሲቲ አማካይ ጄምስ ማዲሰን በቀበሮዎቹ ቤት አዲስ ኮንትራት ሊፈርም ነው።
(Express)





የርገን ክሎፕ የቡድናቸውን ስኳድ ይበልጥ ለማጠናከር በቀጣዩ የውድድር መስኮት ጀርመናዊውን የባየርን ሊቨርኩሰን አማካይ ካይ ሀቨርትዝ ማዘዋወር ይፈልጋሉ።
(Express)





በተለይ በማንቸስተር ዩናይትድ በጥብቅ የሚፈለገው ሴኔጋላዊው የናፖሊ ተከላካይ ካሊዱ ኩሊባሊ በዝውውር ሒሳቡ £128ሚ. መሆኑን ሚረር ገልጿል።
(Mirror)





ጣሊያናዊው የቼልሲ አማካይ ጆርጊንሆ ከቀድሞው አሰልጣኙ ማውሩዚዮ ሳሪ ጋር በጁቬንትስ ለመስራት ፍላጎት እንዳለ'ው ወኪሉ ተናግሯል።
(Mail)





ካሜሮናዊው የአያክስ ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና በፓሪሰን ዤርመን እና ባርሴሎና የሚፈለግ ቢሆንም የእርሱ ምርጫ ግን የእንግሊዙ ክለብ ቼልሲ ነው።
(Caught Offside)





ክሎፕ በውሰት ባየርን ሙኒክ የሚገኘውን የባርሴሎናውን ብራዚላዊ አማካይ ፌሊፔ ኩቲንሆ ወደ ሊቨርፑል መመለስ ይፈልጋሉ።
(Star)

የዕለተ እሁድ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

                   አቅራቢ - ኢብራሒም ሙሐመድ



ማንችስተር ሲቲዎች በቀጣዩ የዝውውር መስኮት ሊዮኔል ሜሲን ማስፈረም እንደሚፈልጉ ዘ ኤክስፕረስ ዛሬ አስነብቧል ዝውውሩ የመሳካት እድል ባይኖረውም ሲቲዎች ግን ፍላጎት አላቸው።



ዩናይትድ እና አስቶንቪላ በጃክ ግሪሊሽ ዝውውር ጉዳይ ተቀምጠው ለመነጋገር ቀጠሮ ይዘዋል ዛሬ በርካታ የእንግሊዝ ጋዜጦች ዩናይትድ ክረምት ላይ ተጨዋቹን እንደሚያስፈርሙት በእርግጠኝነት እየዘገቡ ይገኛሉ።



አርሰናሎች የቀድሞ አሰልጣኛቸውን አርሰን ዌንገርን በሌላ የስራ ሚና ወደ ኢምሬት ለመመለስ እየሰሩ ነው የክለቡ ሰዎች ዌንገርን ለማስማማት ንግግጌ ላይ ናቸው።




በዘንድሮ ሲዝን አርሰናልን ለቆ ወደ ጣሊያኑ ጁቬንቱስ በነፃ የተዘዋወረው አሮን ራምሴ በአሮጊቶቹ ቤት ብዙም የመሰለፍ እድልን እያገኘ አደለም ይህንን ተከትሎ ራምሴ በክረምቱ የዝውውር መስኮን ጁቬን መልቀቅ ይፈልጋል።




ሊቨርፑሎች በግራ ተከላካይ መስመር ያለባቸውን የተጠባባቂ ተጨዋች ችግርን ለመቅረፍ በክረምቱ የዝውውር መስኮት የግራ መስመር ተከላካይ እንደሚያስርሙ ታውቋል።




ባሳለፍነው ክረምት ማንችስተር ዩናይትድ አልያም ቶተንሀም ሊገባ ነው ሲባል የሰነበተው አርጀንቲናዊው ፓብሎ ዲባላ በቱሪን ለተጨማሪ አመት ለመቆየት ወስኗል በጁቬም አዲስ ኮንትራት ለመፈረም ከጫፍ ደርሷል.




ማውሪሲዮ ፖቸቲንሆ አሁንም ፍላጎቱ ዩናይትድ እንደሆነ ሚረር አስነብቧል ከቶተንሀም ከተሰናበተ ቡሀላ ከተለያዩ ክለቦች ጋር ስሙ ሲያያዝ ቢሰነብትም እሱ የሱ ምርጫ ግን አሁንም ዩናይትድ ነው።




የፒኤስጂ ዋና አለቃ ናስር አልካላፊ በምንም አይነት መልኩ በክረምት ክሊያን ምባቤን ለመልቀቅ ለድርድር እንደማይቀመጡ ሲናገሩ በተጨማሪም ተጨዋቹን ተጨማሪ ኮንትራት ለማስፈረም እየሰሩ መሆኑን ይፋ አርገዋል።

የዕለተ እሁድ ከሰዓት ስፖርታዊ ዜናዎች

               አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)


ሰሞኑን የሊዮኔል ሜሲ ስም ከዝውውር ጋር በሰፊው በመያያዝ ላይ ይገኛል።ኤክስፕረስ ዛሬ እንደዘገበው ከሆነ ደግሞ የ32 አመቱ አርጀንቲናዊ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት ወደ ማንቸስተር ሲቲ እንዲመጣ ውሃ ሰማያዊዎቹ ይፈልጋሉ።
(Express)





ጉዳት ላይ የሰነበተው የማንቸስተር ሲቲው አጥቂ ራሂም ስተርሊንግ ክለቡ በሻምፒዮንስ ሊግ ከሪያል ማድሪድ ጋር ላለበት ጨዋታ እንደሚመለስ ይጠበቃል።
(Telegraph)





የቀድሞው የቶተንሃም አሰልጣኝ ማውሩሲዮ ፖቼቲንሆ በዚህ አመት የትኛውንም ክለብ ለማሰልጠን ያልወሰነው በቀጣዩ ማንቸስተር ዩናይትድን ስለሚይዝ ነው ሲል ሚረር አስነብቧል።
(Mirror)





ባለቤትነቱ የባርሴሎና ሆኖ በውሰት ባየርን ሙኒክ የሚገኘው ብራዚላዊው አማካይ ፌሊፔ ኩቲንሆ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት  ማረፊያው ማንቸስተር ሲቲ ወይም የቀድሞው ክለቡ ሊቨርፑል እንደሚሆን ይጠበቃል።
(Express)





ስሙ ከባርሴሎና እና ሪያል ማድሪድ ጋር በስፋት ሲያያዝ የነበረው ቤልጄሚያዊው የማንቸስተር ሲቲ አማካይ ኬቨን ደ ብሮይነ አሁን በኢቲሀድ ደስተኛ መሆኑን ተናግሯል።
(Goal)



በሪያል ማድሪድ አመታትን ያሳለፈው ዌልሳዊው ኢንተርናሽናል ጋሬዝ ቤል ስሙ ከተለያዩ ክለቦች ጋር በተለይም ከቶተንሃም ጋር ቢያያዝም እርሱ ግን ወደ ቻይና የመሄድ ዕድሉ ሰፊ እንደሆነ እየተዘገበ ይገኛል።
(Goal)





በዝውውር መስኮት ስሙ ከማንቸስተር ዩናይትድ እና ቼልሲ ጋር ሲያያዝ የነበረው ኡራጋዊያዊው የፓሪሰን ዤርመን አጥቂ ኤዲንሰን ካቫኒ በአመቱ መጨረሻ በፓርክ ደ ፕሪንስ ያለው ኮንትራት ሲያበቃ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መሄዱ አይቀሬ ነው።
(L'Equipe, via Star)





ከአርሰናል ጁቬንትስን ተቀላቅሎ በቱሪን የተጨዋች ህይወቱን እየገፋ የሚገኘው ዌልሳዊው ኢንተርናሽናል አሮን ራምሴ ከጣሊያን መውጣትን ይሻል።
(Calciomercato - in Italian)





ሊቨርፑል በቀጣዩ የዝውውር መስኮት አንድ የግራ መስመር ተከላካይ እና ጀርመናዊውን የራ.ቢ ሌብዝሽ አጥቂ ቲሞ ዋርነር ማዘዋወር ይፈልጋል።
(Athletic, via Team Talk)

Saturday, February 8, 2020

የዕለተ ቅዳሜ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

                         አቅራቢ  - ኢብራሒም ሙሐመድ


ቶተንሀም እና አርሰናል ሴኔጋላዊውን ተከላካይ ካሊዱ ኩሊባሊን ለማስፈረም ይፈልጋሉ ሁለቱም ክለቦች ከተጨዋቹ ወኪሎች ጋር ንግግር ማድረግ እንደጀመሩ ተሰምቷል።




ሊቨርፑሎች ከሳውዝሀምተንካስፈረሙት ረጅም አመታትን በአንፊልድ የቆየውን እንግሊዛዊውን አዳም ላላን በክረምቱ በነፃ ሊለቁት ነው ምክንያቱም ተጨዋቹ ኮንትራቱ በዚህ አመት ሲጠናቀቅ ሊቨርፑሎች ለልጁ አዲስ ኮንትራት ለመስጠት ፍላጎት የላቸውም።




ቸልሲዎች የአጥቂ መስመር ችግራቸውን ለመቅረፍ በክረምቱ የዝውውር መስኮት የሊዮኑን ሙሳ ዴምቤሌን እና የኢንተር ሚላኑን ላውታሮ ማርቲኔዝን ለማስፈረም ይፈልጋሉ።




ባርሴሎናዎች ለፊሊፕ ኩቲትሆ 80ሚዩ ይፈልጋሉ ይህንን ገንዘብ ለሚያቀርብ ክለብ ልጁን ለመስጠት ፍቃደኛ ናቸው።



£15ሚ. የሚያወጣውን የብሬንትፎርድ የመስመር ተጨዋች ሰኢድ ቤንረህማን ለማስፈረም ሌስተር እና አርሰናሎች ተፋጠዋል።



የቀድሞው የአርሰናል ቶተንሀም እና ማን ሲቲ አጥቂ ኢማኑዬል አዲባየር ለፓራጓዩ ኦሎምፒያ ክለብ ለመጫወት መስማማቱ ታውቋል።




በጥር የዝውውር  ዶርትመንድን የተቀላቀለው የፊት መስመር አጥቂ ኤርሊንግ ሀላንድ የጥር ወር የቡንደስ ሊጋው ምርጥ ተጫዋች በመባል ተመርጧል።




ኢቫንዛሞራ አርትሮ ቪዳል በክረምቱ ወደ ቀድሞ አሰልጣኙ አንቶኒዮ ኮንቴው ጁቬንቱስ ለማምራት እንደተዘጋጀ ይፋ አድርጓል።




ቸልሲ እና ማንዩናይትድ በእንግሊዛዊው የቦሩሲያ ዶርትመንድ የመስመር አጥቂ ዳጀን ሳንቾ ዝውውር ላይ ተፋጠዋል።ዛሬ በወጡ መረጃዎች መሰረት ዩናይትዶች ከቸልሲ የተሻለ ሂሳብ ለማቅረብ ዝግጁ ሆነዋል።

በእግር ኳስ ታሪክ በርካታ ዋንጫ ያሳኩ 20 ክለቦች

በእግር ኳስ ታሪክ በርካታ ዋንጫ ያሳኩ 20 ክለቦች

         አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)





የዓለማችን ውዱ የስፖርት ዘርፍ በሆነው እግር ኳስ ውስጥ በአጠቃላይ ዓለም ላይ በርካታ ሐያላን ክለቦች ይገኛሉ።ለዛሬ ከዓለም ብዙ ዋንጫ በማሳካት ከፊት የሚመሩትን 20 ክለቦች እንጠቁማችኋለን ……… ሰናይ ንባብ!




20.ክለብ ኦሊምፒያ -------- ፓራጓይ ------ 57 ዋንጫዎች


19.FCSB ---------------- ሮማኒያ ------------ 58 ዋንጫዎች


18.ሊቨርፑል -------------እንግሊዝ  ----------- 59 ዋንጫዎች


17.አንደርሌክት ---------- ቤልጂየም ---------- 60 ዋንጫዎች


16.ጋላታሳራይ ----------- ቱርክ ------------------- 61 ዋንጫዎች


15.ጁቬንትስ -------------- ጣሊያን ---------------- 63 ዋንጫዎች



14.ባየርን ሙኒክ ----------- ጀርመን ----------------- 70 ዋንጫዎች



13.አያክስ ------------------ ኔዘርላንድ ------------------ 70 ዋንጫዎች



12.ማንቸስተር ዩናይትድ ------- እንግሊዝ ------------- 71 ዋንጫዎች



11.አል-ፋይሰሊ --------------- ዮርዳኖስ ---------------- 74 ዋንጫዎች



10.ፖርቶ ------------------- ፖርቱጋል------------------- 74 ዋንጫዎች



9.ኦሊምፒያኮስ ------------ ግሪክ ------------------------- 75 ዋንጫዎች



8.ቤኔፊካ ------------------ ፖርቱጋል ---------------------- 82 ዋንጫዎች



7.ሪያል ማድሪድ ------------- ስፔን ----------------------- 90 ዋንጫዎች



6.ባርሴሎና ----------------- ስፔን ----------------------- 91 ዋንጫዎች



5.ሴልቲክ ------------------- ስኮትላንድ --------------- 105 ዋንጫዎች



4.አትሌቲኮ ፔናሮል -------- ኡራጓይ ----------------- 108 ዋንጫዎች



3.ክለብ ናሲዮናል ደ ፉትቦል -------- ኡራጋይ ---------- 113 ዋንጫዎች



2.ሬንጀርስ ---------------- ስኮትላንድ ------------- 115 ዋንጫዎች



1.አል-አህሊ ------------- ግብጽ ----------------- 118 ዋንጫዎች

የዕለተ ቅዳሜ ስፖርታዊ ዜናዎች

           አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)

የሀገር ውስጥ ዜናዎች
የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ በዚህ ሳምንት ሲቀጥል የተለያዩ ጨዋታዎች ይደረጋሉ።የ13ተኛውን ሳምንት ሙሉ ፕሮግራም እነሆ :

ቅዳሜ
መቐለ 70 አ. ከ ፋሲል ከነማ - 9:00

እሁድ
ሀዋሳ ከተማ ከ ጅማ አባ ጅፋር - 9:00
ወልዋሎ ዓ.ዩ. ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ - 9:00
ድሬደዋ ከተማ ከ ስሑል ሽረ - 9:00
ባህር ዳር ከተማ ከ ሰበታ ከተማ - 9:00

ሰኞ
ሲዳማ ቡና ከ ሀዋሳ ከተማ - 9:00

ማክሰኞ
ሀዲያ ሆሳዕና ከ ወላይታ ድቻ - 9:00

ሐሙስ
ኢትዮጵያ ቡና ከ ወልቂጤ ከተማ

ምንጭ  - ሶከር ኢትዮጵያ




የውጭ ስፖርታዊ ዜናዎች



በበርካታ ሀያላን ክለቦች የሚፈለገው ሴኔጋላዊው የናፖሊ ተከላካይ ካሊዱ ኩሊባሊ በአመቱ መጨረሻ በተለይ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ የመሄድ ዕድሉ ከፍተኛ ነው።
(Star)





ባርሴሎና በውሰት ለባየር ሙኒክ ሰጥቶት የነበረውን ብራዚላዊውን አማካይ ፌሊፔ ኩቲንሆ በአመቱ መጨረሻ መሸጥ ይፈልጋል።የዝውውር ዋጋውም £67ሚ. እንደሚሆን ተጠቅሷል።
(Mundo Deportivo - in Spanish)






ቼልሲ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት አርጀንቲናዊውን የኢንተር ሚላን አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ እና የሊዮኑን ፈረንሳዊ አጥቂ ሞሳ ዴምቤሌ ለማዘዋወር ይሰራል።
(Evening Standard)





ባርሴሎና የቀድሞውን ተጨዋቹን አዳማ ትራኦሬን ከዎልቭስ ለማዘዋወር ፍላጎት ያለው ቢሆንም ሪያል ማድሪድ ሳንካ እንዳይሆንበት ይሰጋል።
(Mail)






ቦሩሲያ ዶርትመንድ እንግሊዛዊውን አጥቂ ጄደን ሳንቾ ከዩሮ 2020 በፊት መሸጥ አይፈልግም።ምክንያቱ ደግሞ የ19 አመቱ ተጨዋች ከውድድሩ በኋላ ዋጋው ከፍ ይላል በሚል ግምት ነው።
(90min)





ሊቨርፑል በአመቱ መጨረሻ ኮንትራቱ ለሚያበቃው እንግሊዛዊው አማካይ አዳም ላላና አዲስ ኮንትራት አላቀረበለትም።በዚህም ይህ አመት ሲያልቅ ወደ ፈለገበት ክለብ በነጻ የሚጓዝ ይሆናል።
(Liverpool Echo)





ቼልሲ የእንግሊዛዊውን የ18 አመት አማካይ ቲኖ አንጆሪን እና የሆናላንዳዊውን የ17 አመት ታዳጊ ተከላካይ ላን ማትሰን ውል ለማራዘም በመስራት ላይ ነው።
(Mail)





ጁቬንትስ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ለማዘዋወር በጥብቅ ከሚፈልጋቸው ተጨዋቾች መሀከል የቼልሲው ጣሊያናዊ የግራ መስመር ተከላካይ ኤመርሰን ፓልሜሪ አንዱ ነው።
(Inside Futbol)

Friday, February 7, 2020

የዕለተ አርብ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

                  አቅራቢ  - ኢብራሒም ሙሐመድ



አርሰናሎች በክረምቱ የዝውውር መስኮት ቱርካዊውን አማካይ ኡርኩን ኮኩን ለማስፈረም ፍላጎት አላቸው ባሳለፍነው ሳምንት መልማዮችን ወደ ሆላንድ በመላክ ልጁን መመልከታቸው ተሰምቷል።




በጉዳት ምክንያት በቶተንሀሙ ጨዋታ ላይ ተቀይሮ የወጣው ራሂም ስተርሊንግ ከጉዳቱ ባለማገገሙ ከእሁዱ የኢትሀዱ የዌስትሀም ጨዋታ ውጭ መሆኑን ፔፕ ይፋ አድርጓል።




የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የጥር ወር ኮከቦችን ይፋ አድርጓል በኮከብ አሰልጣኝነት የርገን ክሎፕ በኮከብ ተጨዋችነት ኩን አጉዌሮ እንዲሁም በምርጥ ጎል የብራይተኑ አሊሬዛ ጃሀንባካሽ ሆነው ተመርጠዋል።




ሪያል ማድሪድ እና ባርሴሎና በ24 አመቱ የወልቭስ የመስመር አጥቂ አዳማ ትራኦሬ ዝውውር ላይ ተፋጠዋል ወልቭሶች ከልጁ እስከ £90m ይፈልጋሉ።





ዩናይትዶች በክረምቱ አጥቂ ለማስፈረም ወደ ገበያ እንደሚወጡ እውን ሆኗል ዩናይትዶችም ዋና ኢላማ ያረጉት ላውታሮ ማርቲኔዝ ላይ ትኩረት አድርገዋል ኢንተር ሚላኖች ከተጨዋቹ እስከ £94m ይፈልጋሉ።




ቡድኑን በአዲስ መልክ ለመገንባት እቅድ ያለው የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚካኤል አርቴታ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ሶስት ቋሚ ተጨዋቾችን ለሽያጭ አቅርበዋል ተጨዋቾቹም ኦዚል ላካዜቲ ኦባምያንግ ናቸው።





ጁቬንቱሶች ከትናንት ጀምሮ ከባርሴሎና ጋር ሊለያይ ነው የተባለውን ሊዮኔል ሜሲ ለማስፈረም ይፈልጋሉ። ሜሲን ለማስፈረም ብዙ ገንዘብ ቢያስፈልግም ጁቬዎች ግን ያወጣውን አውጥተው ሜሲን ለማስፈረም ይፈልጋሉ።




ቶተንሀሞች የፊት መስመር ተጨዋቹን ትሮይ ፓሮትን ኮንትራት አራዝመዋል በአዲሱ ውል መሰረት ትሮይ  ፓሮት እስከ 2023 በቶተንሀም ይቆያል።

የዕለተ አርብ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች

አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)



ማንቸስተር ዩናይትድ ለፖል ፖግባ ከዚህ በፊት ከመደበው ገንዘብ ላይ £30ሚ. መቀነሱ ታውቋል።በኦልድ ትራፎርድ ደስተኛ እንዳልሆነ በተደጋጋሚ የተነገረለት ፈረንሳዊ ኢንተርናሽናል አሁን የመ'ሸጫ ዋጋው ወደ £150ሚ. ዝቅ ብሏል።
(Sun)





አዲሱ የአርሰናል አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ስኳዱን ለማጠናከር በቅርቡ የአሌክሳንደር ላካዜት ፣ ሜሱት ኦዚል እና ፔር ኤምሪክ ኦባማያንግ ጉዳይን መስመር ማስያዝ ይፈልጋል።
(Sun)





ባርሴሎና በቀጣዩ የዝውውር መስኮት የዎልቭሱን አጥቂ አማዳ ትራኦሬ ለማዘዋወር ይፈልጋል።ትራኦሬ ላማሲያ ውስጥ ማደጉ ይታወሳል።
(Mail)





አርጀንቲናዊው የኢንተር ሚላን አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት ከባርሴሎና ይልቅ ማንቸስተር ዩናይትድን አሊያም ማንቸስተር ሲቲን መቀላቀል ይፈልጋል።
(Star)





ፍራንክ ላምፓርድ በኬፓ አሪዛባልጋ ደስተኛ ባለመሆኑ ካሜሮናዊውን የአያክስ ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና ለማዘዋወር ይፈልጋል።
(Goal.com)



ስሙ ከፓሪሰን ዤርመን ጋር በስፋት ሲያያዝ የሰነበተው ብራዚላዊው የሪያል ማድሪድ ታዳጊ ቪኒሺየስ ጁኒየር በሳንቲያጎ በርናቢዮ መቆየት እንደሚፈልግ ተናግሯል።የ19 አመቱ ብራዚላዊ 2018 ላይ ነበር ሎስብላንኮዎቹን የተቀላቀለው።
(Goal)





በአመቱ መጨረሻ በሊቨርፑል ያለው ውል የሚጠናቀቀው አዳም ላላና ከቀድሞው አሰልጣኙ ብሬንደን ሮጀርስ ጋር ሊገናኝ እንደሚችል ተዘግቧል።ይህም የሚሆነው ደግሞ እንግሊዛዊው አማካይ ወደ ሌስተር ሲቲ ከተዘዋወረ ነው።
ላላናን ከሌስተር በተጨማሪ ቶተንሃም ፣ አርሰናል እና ዌስት ሀም ይፈልጉታል።
(The Telegraph)





የ2020/2021 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበት ቀን ይፋ ሆኗል ቀኑም ነሀሴ2 በእለተ ቅዳሜ እንደሚጀመር ይፋ ሲደረግ ነሀሴ 26 ደሞ የዝውውር መስኮት እንደሚጠናቀቅ ይፋ ተደርጓል።




ባርሴሎናዎች የጌታፌውን አጥቂ አንጀል ሮድሪጌዝን ለማስፈረም እንቅስቃሴ ጀምረዋል ባርሳዎች የኡስማን ዴምቤሌን ተደጋጋሚ ጉዳት ተከትሎ ተጨዋቹን ማስፈረም ፈልገዋል።




ማንችስተር ሲቲዎች በሊሮይ ሳኔ ዝውውር ላይ ተስፋ ቆርጠዋል ተጨዋቹ አዲስ ወኪል መያዙ ይፋ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ሳኔም ወኪሉን የቀየረው ክረምት ላይ የባየርን ሙኒኩን ዝውውሩን ስላላጠናቀቀለት ነበር ።







Thursday, February 6, 2020

የዕለተ ሐሙስ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

               አቅራቢ - ኢብራሒም ሙሐመድ



የ2020/2021 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበት ቀን ይፋ ሆኗል ቀኑም ነሀሴ2 በእለተ ቅዳሜ እንደሚጀመር ይፋ ሲደረግ ነሀሴ 26 ደሞ የዝውውር መስኮት እንደሚጠናቀቅ ይፋ ተደርጓል።




ባርሴሎናዎች የጌታፌውን አጥቂ አንጀል ሮድሪጌዝን ለማስፈረም እንቅስቃሴ ጀምረዋል ባርሳዎች የኡስማን ዴምቤሌን ተደጋጋሚ ጉዳት ተከትሎ ተጨዋቹን ማስፈረም ፈልገዋል።




ማንችስተር ሲቲዎች በሊሮይ ሳኔ ዝውውር ላይ ተስፋ ቆርጠዋል ተጨዋቹ አዲስ ወኪል መያዙ ይፋ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ሳኔም ወኪሉን የቀየረው ክረምት ላይ የባየርን ሙኒኩን ዝውውሩን ስላላጠናቀቀለት ነበር ።




አንድሬያ ርሞሌንኮ በክረምት ዌስትሀምን ለመልቀቅ ተቃርቧል ተጨዋቹ ተደጋጋሚ ጉዳት እና እድሜ ተጨምሮበት እንዲሁም ሞይስ ዌስትሀምን በወጣት ተጨዋቾች ለመገንባት ማሰቡን ተከትሎ ልጁ ሊለቅ ነው።





የዶርትመንዱ ሊቀመንበር ማይክል ዞርክ በጥር ላይ ስሙ በተደጋጋሚ ከቸልሲ እና ከዩናይትድ ጋር ሲያያዝ ስለነበረው ጄደን ሳንቾ ተጠይቀው ጥር ላይ ምንም አይነት ጥያቄ እንዳልቀረበላቸው ይፋ አድርገዋል ።




ማንችስተር ሲቲዎች በክረምቱ ሶስት ተጨዋቾች ለማስፈረም ሚፈልጓቸውን ተጨዋቾች ይፋ ሲያደርጉ ሮቢን ኔቬስን ከወልቭስ ካሊዱ ኩሊባሊን ከናፖሊ ኤርሊንግ ሀላንድን ከዶርትመንድ መሆናቸው ታውቋል።




የአርሰናሉአሰልጣኝ ማይክል አርቴታ ከ2020 የአውሮፓ ዋንጫ በፊት ሶስት ተጨዋቾችን እንዲያስፈርሙላቸው እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።




ወልቭሶች ለአዳማ ትራኦሬ ሪከርድ የሆነ የግዢ ጥያቄ ሚቀርብላቸው ከሆነ ለመሸጥ ዝግጁ ሆነዋል።

Wednesday, February 5, 2020

የዕለተ ሐሙስ ማለዳ ስፖርታዊ ዜናዎች

አቅርቢ - ኢብራሒም ሙሐመድ





እንግሊዛዊው ኮከብ ሀሪ ኬን ወደ ሜዳ የመመለሻው ጊዜ ከታሰበበት ጊዜ እንደሚዘገይ ተረጋግጧል ኬን ለ2020 የአውሮፓ ዋንጫ የመድረስ እድሉ ሰፊ ሲሆን ለቶተንሀም ግን በዚህ አመት ግልጋሎት ላይሰጥ ይችላል።





ማርኮ ሪዩስ ዶርትመንዶች ከፒኤስጂ ጋር ላለባቸው የቻምፒየንስ ሊግ አንደኛ ዙር ጨዋታ አይደርስም ዶርትመንድ ማክሰኞ እለት በብሬመን ሲሸነፍ ጉዳት ያስተናገደው ሮይስ እስከ አራት ሳምንት ከሜዳ ይርቃል።




ለረጅም ጊዜ በጉዳት ምክንያት የራቀው ወጣቱ የቸልሲ አማካይ ሩበን ሎፍተስቺክ በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ተረጋግጧል ባሳለፍነው ሳምንትም ከB ቡድኑ ጋር ልምምድ እና ቼልሲ ከብሬድፎርድ B ቡድን ጋር ባደረገው ጨዋታ ተሰልፏል።




አትሌቲኮ ማድሪዶች ከቶተንሀም ከለቀቁ ቡሀላ ያለ ስራ የተቀመጡትን ማውሪሲዮ ፖቸቲንሆን ዳግም ወደ ስፔን ለመመለስ ፍላጎት አላቸው ከዲያጎ ሲሞኒ ጋር ኮንትራት ቢኖራቸውም የሲሞኒን ኮንትራት ክረምት ላይ በማቋረጥ ፖቸቲትሆን መቅጠር ይፈልጋሉ።




ሪያል ማድሪዶች የፈረንሳዊውን ኮከብ ኪሊያን ምባፔ የመሸጫ ዋጋ እስኪቀንስ እንደሚታገሱት እና ልጁን 2021 ላይ £150m ብቻ ከፍለው እንደሚያስፈርመት ተማምነዋል።





ጣሊያናዊው የቸልሲ አማካይ ጀርጊንሆ ከናፖሊ ወደ ቼልሲ ያመጡትን ማውሪዚዮ ሳሪን በድጋሚ አብሯቸው ለመስራት ወደ ጁቬንቱስ ለመዘዋወር እንደሚፈልግ ተሰምቷል።




ጀርመናዊውየሲቲየመስመርተጨዋች ሊሮይ ሳኔ በክረምቱ የዝውውር በጥብቅ ወደ ሚፈልገው ክለብ ባየርን ሙኒክ መዘዋወር እንደሚፈልግ ለጓደኞቹ ነግሮዋቸዋል።

Tuesday, February 4, 2020

የዕለተ ረቡዕ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች

አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)



ዛሬ ክርስቲያኖ ሮናልዶ 35ተኛ አመቱን ደፍኗል።እስቲ ስለዚህ ፖርቱጋላዊ አንድ ሁለት እንበል ……

ከእያንዳንዱ ስኬታማ ሰው ዛሬ ጀርባ በርካታ ከባድ እና አታካች ትናንቶች አልፈዋል።

አስተዳደጉ በፈተናዎች የተሞላ ነበር።ምግብ ከበርገር ቤት ለምኖ ከጓደኞቹ ጋር የተመገበባቸው ቀናት እልፍ ነበሩ።በአስራዎቹ አጋማሽ ሳለም ከባድ የልብ ህመም አጋጥሞት 'ከዚህ በኋላ እግር ኳስን እርም በል' ቢባልም በእናቱ አጋዥነት ከቀዶ ጥገና በኋላ በርትቶ በመስራት አሁን ያለበት ደረጃ ደርሷል።ታዳጊ ሳለ ለጓደኞቹ 'አንድ ቀን የዓለማችን ምርጡ ተጨዋች እሆናለሁ' ሲላቸው አፊዘውበታል ፥ አሁን በዚህ ሀሳብ የሚስማሙ ሚሊየኖች ናቸው።
ይህ አሁን በሰውነቱ ቅርጽ ብዙዎች የሚደመሙበት ሰው በታዳጊነቱ ጓደኞቹ በቀጫጫነቱ የሚሳለቁበት ሰው ነበር።

አሁን ይህ ሰው በግሉም ፣ ከክለብ ጋር እንዲሁም ከሀገሩ ጋር ስሙን በወርቅ ብዕር ጽፏል።የአምስት ባሎንዶሮች እንዲሁም የእልፍ አዕላፍ ስኬቶች ባለቤት ነው።አለም ላይ እግርህ እስኪኳትን ብትዞር 'ክርስቲያኖ ሮናልዶ' የሚለው ስም የማይታወቅበት ሀገር ልታገኝ አትችልም።

ዛሬ ሮናልዶ 35ተኛ አመቱን ያከብራል።ይህ ከሜዳ ውጪ በሰብዓዊነቱ እጅጉን የሚሞገሰው ፖርቱጋላዊ እግር ኳስን ሊሰናበት ጥቂት አመታት ብቻ እንደቀሩት ስናስብ ልባችንን ሀዘን ይሞላዋል።

መልካም ልደት ፥ ክርስቲያኖ!



የዝውውር ዜናዎች



ፈረንሳዊው የማንቸስተር ዩናይትድ አማካይ ፖል ፖግባ ለቡድን አጋሮቹ አሁንም ቀያይ ሰይጣኖቹን መልቀቅ እንደሚፈልግ እና በጥር ወሩ የዝውውር መስኮት እንደሚሆንም ነግሯቸዋል።
(Manchester Evening News)





ጁቬንትስ ጀርመናዊውን የማንቸስተር ሲቲ የክንፍ አጥቂ ለሮይ ሳኔ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት ለማዘዋወር ዕቅድ አለው።የ24 አመቱ  ተጨዋች በባየርን ሙኒክም ይፈለጋል።
(Calcio Mercato, via Inside Futbol)





የቼልሲ ማኔጅመንት ለፍራንክ ላምፓርድ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት £150ሚ. ለተጨዋቾች ዝውውር የሚበጅትለት ሲሆን ዋነኛው የላምፓርድ ዕቅድ ደግሞ የሊዮኑ ፈረንሳዊ አጥቂ ሞሳ ዴምቤሌ ነው።
(Evening Standard)





በዘንድሮው አመት የመሀል ተከላካይ ክፍሉ የሳሳው ማንቸስተር ሲቲ ሁለት ተከላካዮችን ለማስፈረም አቅዷል።በጆን ስቶንስ አቋሚ ደስተኛ ያልሆነው ፔፕ ጋርዲዮላ ዋነኛ ለማጠናከር የሚፈልገው ስፍራ ተከላካይ መስመሩን ነው።
(Times, subscription required)





የዌልሳዊው የሪያል ማድሪድ ኮከብ ጋሬዝ ቤል ወኪል ለ30 አመቱ ተጨዋች በጥር ወር የዝውውር መስኮት ከቶተንሃም ምንም አይነት የዝውውር ጥያቄ እንዳልቀረበ ተናግሯል።
(Talksport)





በተደጋጋሚ ከባርሴሎናጋር ስሙ እየተነሳ የሚገኘው ብራዚላዊው ኮከብ ዊሊያን ኮንትራቱ በዚህ አመት ይጠናቀቃል ሆኖም ዊሊያን ወደ ባርሴሎና ከማምራት ይልቅ በቸልሲ በተጨማሪ አዲስ ኮንትራት ለመፈረም ፍላጎት አለው።






በጉዳትለረጅምጊዜያት የራቀው ፖግባ እና በፈረንጆቹ አዲስ አመት ዋዜማ ላይ ጉዳት ያስተናገደው ስኮት ማክቶሚናይ ለስታንፎርዱ ብሪጅ ጨዋታ እንደሚደርሱ ሶልሻየር አረጋግጧል።





ጄራርድ ፒኬ እሁድ እለት ሌቫንቴን ሲያሸንፉ ቢጫ ካርድ ተመልክቶ ነበር ይህንንም ተከትሎ በቀጣይ ባርሴሎና ሪያል ቤትስን ሲገጥም በቅጣት ማይኖር ይሆናል።

የዕለተ ማክሰኞ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች


አቅራቢ  - ኢብራሒም ሙሐመድ




M.E.Nዛሬከሰአት ባወጣው መረጃ ከሆነ ፖል ፖግባ በክረመቱ የዝውውር መስኮት ከዩናይትድ መልቀቁ አይቀሬ እንደሆነ አስነብቧል።




በቸልሲቦርድእና በፍራንክ ላምፓርድ መካከል በስፔናዊው ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋ ጉዳይ አለመግባባታቸው ታውቋል ላምፓርድ ተጨዋቹ እንዲሸጥ ይፈልጋል።




ባሳለፍነውሳምንትክሊያን ምባፔ እና አሰልጣኙ ተቀይሮ ሲወጣ መጋጨታቸው ይታወሳል ሆኖም አንዳንድ ጋዜጦች ልጁን ከሊቨርፑል እና ከማድሪድ ጋር ስሙን ሲያያዙ ቆይተዋል አሁን ላይ ግን ወኪሉ እንደተናገረው ከሆነ ምባፔ ከክለቡ እንደማይለቅ ተናገረ።




ዌልሳዊውየማድሪድአጥቂ ጋሪዝ ቤል ከማድሪድ ሲለቅ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከማምራት ይልቅ ወደ አሜሪካው ሜጀር ሊግ ሶከር ወይም ወደ ቻይና ሊጓዝ እንደሚልግ ተሰምቷል።




በጉዳትእየተቸገረየሚገኘው ኡስማን ዴምቤሌ በልምምድ ላይ ሳለ በድጋሚ ጉዳት አስተናግዷል  የጉዳቱ መጠን ባይታወቅም ጉዳቱ ግን በድጋሚ የጡንቻ መሳሳብ እንደሆነ ተነግሯል።




በተደጋጋሚከባርሴሎናጋር ስሙ እየተነሳ የሚገኘው ብራዚላዊው ኮከብ ዊሊያን ኮንትራቱ በዚህ አመት ይጠናቀቃል ሆኖም ዊሊያን ወደ ባርሴሎና ከማምራት ይልቅ በቸልሲ በተጨማሪ አዲስ ኮንትራት ለመፈረም ፍላጎት አለው።




በጉዳትለረጅምጊዜያት የራቀው ፖግባ እና በፈረንጆቹ አዲስ አመት ዋዜማ ላይ ጉዳት ያስተናገደው ስኮት ማክቶሚናይ ለስታንፎርዱ ብሪጅ ጨዋታ እንደሚደርሱ ሶልሻየር አረጋግጧል።



ጄራርድ ፒኬ እሁድ እለት ሌቫንቴን ሲያሸንፉ ቢጫ ካርድ ተመልክቶ ነበር ይህንንም ተከትሎ በቀጣይ ባርሴዎና ሪያል ቤትስን ሲገጥም በቅጣት ማይኖር ይሆናል።

Monday, February 3, 2020

የዕለተ ማክሰኞ ረፋድ ስፖርታዊ ዜናዎች

                    አቅራቢ- አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)


የቼልሲው አሰልጣኝ ፍራንክ ላምፓርድ ከክለቡ አመራሮች ጋር በግብ ጠባቂው ኬፓ አሪዛባላጋ ቆይታ ዙሪያ አለመግባባታቸውን ሚረር አስነብቧል።
(Mirror)





እንግሊዛዊው የማንቸስተር ዩናይትድ ተጨዋች ሄሴ ሊንጋርድ ከክለቡ የሚለቅ ከሆነ አትሌቲኮ ማድሪድ ወይም ሮማ ማረፊያው እንደሚሆን ይጠበቃል።
(ESPN)





በሊቨርፑል ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ቼልሲ በጥብቅ የሚፈለገው ቲም ወርነር "ወደ ተገቢው ክለብ ለመዘዋወር" እንደሚፈልግ ተናግሯል።ጀርመናዊው አጥቂ በዘንድሮው አመት በሁሉም የውድድር አይነቶች ለራ.ቢ ሌብዚኽ 25 ግቦችን አስቆጥሯል።
(Kicker - via Evening Standard)





ዌልሳዊው የሪያል ማድሪድ አጥቂ ጋሬዝ ቤል ሎስብላንኮዎቹን ሲለቅ ከፕሪሚየር ሊግ ይልቅ ወደ ሜጀር ሊግ ሶከር አሊያም ወደ ቻይና ሱፐር ሊግ ሊጓዝ የሚችልበት ዕድል ሰፊ ነው።
(Star)





አርሰናል እና ኤቨርተን በጥር ወሩ የዝውውር መስኮት የሊሉን ተከላካይ ጋብሬል ለማዘዋወር ሞክረው ሳይሳካ ቀርቷል።
(Le10Sport - in French)





ሰሞኑን ከአሰልጣኙ ቶማስ ቱሀል ጋር የተጋጨው የፓሪሰን ዤርመኑ አጥቂ ኪልያን ምባፔ ወኪል ፈረንሳዊው ተጨዋች ከክለቡ እንደማይለቅ ተናግሯል።ሆኖም የ21 አመቱ ኮከብ ስም በስፋት ከሪያል ማድሪድ ጋር በመያያዝ ላይ ይገኛል።
(Mundo Deportivo - in Spanish)





የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ ሌጀንድ ሪያን ጊግስ ቀያይ ሰይጣኖቹ ፖርቱጋላዊውን አማካይ ብሩኖ ፈርናንዴዝ ማዘዋወራቸው መልካም እንደሆነ ተናግሯል።
(Sun)





ሊቨርፑል ለሆላንዳዊው ተከላካይ ቫርጅል ቫን ዳይክ እና ብራዚላዊ ግብ ጠባቂ አሊሰን ቤከር አዲስ ኮንትራት አቅርቦላቸዋል።ተጨዋቾቹ በሊቨርፑል ቤት ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ይታወቃል።
(Independent)





ኢንተር ሚላን አልጄሪያዊውን አጥቂ ኢስላም ስሌማኒ ከሌስተር ሲቲ ለማዘዋወር ተቃርቧል።አንቶኒዮ ኮንቴ ቡድኑን ለማጠናከር በርካታ ተጨዋቾችን በማስፈረም ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል።
(Calciomercato - in Italian)

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...