Thursday, December 24, 2020

የሳዲዮ ማኔ ድንቅ አስተሳሰብ


 


እንደ አብዛኛዎቹ አፍሪካውያን ማኔ በድህነት ውስጥ ያደገ ነው።ይህ አሁን

በሚሊዮን ፓውንዶች በየአመቱ የሚያገኘው ሴኔጋላዊ ልጅነቱ እምብዛም

አስደሳች አልነበረም።ሆኖም አሁን ያ ጊዜ አልፎ ሀገሩን እና ያሳደገውን አካባቢ

በቻለው አቅም ሁሉ እየረዳ ነው።ማኔ ስለዚህ ጉዳይ ሲጠየቅ እንዲህ አለ ፡

"አስር ፌራሪ መኪና ፣ ሀያ የዳይመንድ ሰዓቶች ፣ ወይም ሁለት አውሮፕላን ለኔ

ምን ያደርግልኛል? እነዚህ ቁሶች ለእኔ እና ለተቀረው ዓለም ምን ያደርጋሉ?

"በልጅነቴ የረሀብ ጊዜያትን አሳልፌያለሁ።ከባባድ ጊዜያትን አልፌያለሁ ።እግር

ኳስን በባዶ እግሬ ነበር የምጫወተው ፥ በድህነት ምክንያት ትምህርት መማር

አልቻልኩም ፥ ብቻ ብዙ ብዙ።ነገር ግን አሁን ያ ሁሉ አልፎ ምስጋና ከእግር ኳስ

ይሁንና ከራሴ አልፌ ሕዝቤንም እረዳለሁ።

"በሀገሬ ትምህርት ቤቶችን ፣ ስቴዲየም ሰርቻለሁ።ልብስ ፣ ጫማ እና ምግብ

ደግሞ ከፍተኛ ድህነት ውስጥ ላሉት እሰጣለሁ።ኑሮዋቸውን እንዲያሻሽሉ

በተወለድኩበት መንደር ለሚገኙ ሰዎች ለየቤተሰቡ በወር 70 ዩሮ እሰጣለሁ።

"እናም እኔ ቅንጡ መኪናዎች ፣ ቅንጡ ቤት ፣ መዝናናት እና አውሮፕላን ምናምን

አልፈልግም።ከዚ ይልቅ በሕይወት አጋጣሚ ካገኘሁት ለሕዝቤ ባካፍክ

እመርጣለሁ።"

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...