Tuesday, November 24, 2020

የዕለተ ማክሰኞ ስፖርታዊ ዜናዎች

አዘጋጅ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች በዚህ ሳምንት የሚደረጉ ሲሆን በዛሬው ዕለት ስምንት ጨዋታዎች ይደረጋሉ 

 

ክራስኖዳር ከ ሲቪያ (2:55) 

ሬንስ ከ ቼልሲ (2:55) 

ቦሩሲያ ዶርትመንድ ከ ክለብ ብሩዥ (5:00) 

ላዚዮ ከ ዜኒት ፒተርስበርግ (5:00) 

ዳይናሞ ኪዬቭ ከ ባርሴሎና (5:00) 

ዩቬንትስ ከ ፍሬንካቭሮቭ (5:00) 

ማን ዩናይትድ ከ ኢስታንቡል ባሳክሄር (5:00) 

ፓሪ ሴንት ዤርመን ከ ሌብዚኽ (5:00)





በዘንድሮው ሲዚን ደካማ ጊዜን እያሳለፈ የሚገኘው እና አዲስ ኮንትራት የፈረመው ፔፕ ጓርዲዮላ ፥ አዲስ ለመስራት ያሰበውን ቡድን ለማጠናከር ፥ የአስቶን ቪላውን እንግሊዛዊ አማካይ ጃክ ግሪሊሽ ለማዘዋወር ይፈልጋል። 

(Independent) 

 

 

 

 

 

የሊዮኔል ሜሲ እህል ውሃ በካምፕ ኑ እያበቃለት ይመስላል።ከአዲሱ አሰልጣኝ ሮናልድ ኪውመን ጋር እምብዛም ያልተጣጣመው ሜሲ ቀጣይ ማረፊያው ማንቸስተር ሲቲ እንደሚሆን እየተነገረ ነው። 

(Times - subscription only) 

 

 

 

 

 

በማን ዩናይትድ ተጠባባቂ ግብ ጠባቂ የሆነው ዲን ሄንደርሰን ከክለቡ መልቀቅ እንደሚፈልግ ሲነገር የቆየ ቢሆንም ኦሌ ጉናር ሶልሻየር ተጨዋቹ በኦልድ ትራፎርድ ይቆያል ብሏል። 

 (Sky Sports) 

 

 

 

 

 

ፍራንክ ላምፓርድ ፈረንሳዊው አጥቂ ኢሊቪየር ዢሩ ለቼልሲ ቁልፍ ተጨዋች መሆኑን ተናገረ።ዢሩ ከስታንፎርድ ብሪጅ እንደሚለቅ ሲነገር ቆይቷል። 

(Mirror) 

 

 

 

 

 

ምንም እንኳን የስፔናዊው አማካይ ኢስኮ ስም በብዛት ከማን ሲቲ እና አርሰናል ጋር ቢያያዝም ፥ ሪያል ማድሪድ እስካሁን ከየትኛውም ክለብ ይፋዊ ጥያቄ አይቀረበለትም። 

(AS) 

 

 

 

 

 

ቦሩሲያ ዶርትመንድ ዴንማርካዊውን አማካይ ክርስቲያን ኤሪክሰን ከኢንተር ሚላን ማዘዋወር ይፈልጋል።ዶርትመንድ ከዚህ በፊት ቶተንሃም እያለም ኤሪክሰንን ይፈልገው ነበር። 

(Tuttermercatoweb - in Italian) 

 

 

 

 

 

ከሊድስ ጋር በነበረው ጨዋታ በቀይ ካርድ የተሰናበተው ኒኮላስ ፔፔ ላሳየው ያልተገባ ባሕሪ ይቅርታ ጠይቋል። 

(Sun)

 

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...