ሪያል ማድሪድ እና ኢንተር ሚላን የኔዘርላንዳዊው አማካይ ጆርጂንሆ ቫይናልደም ፈላጊ ቢሆኑም ሊቨርፑል ግብ ተጨዋቹን በአንፊልድ ለማቆየት ይፈልጋል።
(Mundo Deportivo - in Spanish)
ስፔናዊው የ34 ዓመት ተከላካይ ሰርጂዮ ራሞስ በሪያል ማድሪድ ያለውን ውል አለማራዘሙን ተከትሎ በርካታ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች እየፈለጉት ነው።
(90min)
ሪያል ማድሪድ ሰርጂዮ ራሞስ በክለቡ ቢቆይም ባይቆይም ኦስትሪያዊውን ተከላካይ ዴቪድ አላባ ከባየርን ሙኒክ ማዘዋወር ይፈልጋል።
(Marca)
ኤቨርተን በጥር ወር የዝውውር መስኮት ዌልሳዊውን የመስመር አጥቂ ዳኔል ጄምስ ለማዘዋወር አቅዷል።
(Football Insider)
የዩቬንትሱ አማካይ ሳሚ ኬዲራ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ለመጓዝ ፍላጎት ያለው ሲሆን ኤቨርተን እና ማንቸስተር ዩናይትድ ደግሞ ፈላጊዎቹ ናቸው።
(Sun)
ኤርሊንግ ሀላንድ ከቦሩሲያ ዶርትመንድ ጋር ዋንጫዎቹ ለማሳካት እንጂ ክለቡን ከመልቀቅ ዕቅድ እንደሌለው አባቱ አሳውቋል።
(Sport1, via Goal)
ፔፕ ጓርዲዮላ ለተጨማሪ አመታት በኤቲሀድ ለመቆየት መስማማቱን ተከትሎ ፡ ማን ሲቱ አርጀንቲናዊውን ምትሀተኛ ሊዮኔል ሜሲ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት ለማዘዋወር ለፔፕ ቃል ገብቶለታል።
(Mirror)
ማንቸስተር ዩናይትድ ፣ ፓሪሰን ዤርመን እና ሪያል ማድሪድ ፈረንሳዊውን የሬንስ አማካይ ኤድዋርዶ ካራቪንጋ ለማዘዋወር ፉክክር ውስጥ ገብተዋል።
(Marca - in Spanish)
ቨርጅል ቫን ዳይክ የጉልበት ቀዶ ጥገና ካደረገ በኋላ ቀለል ያሉ ልምምዶችን መስራት ጀምሯል።በዚህ ሲዝን ወደ ሜዳ ሊመለስም ይችላል።
(Mail)
No comments:
Post a Comment