Sunday, April 26, 2020

ማክቶሚናይ ከቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትዱ ታላቅ ተጨዋች ሮናልዶ የወሰደውን ትምህርት ተናግሯል

                 አዘጋጅ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)



በማን ዩናይትድ ቤት ድንቅ ጊዜን እያሳለፈ የሚገኘው ስኮትላንዳዊው አማካይ ስኮት ማክቶሚናይ ከ2003 እስከ 2009 በኦልድ ትራፎርድ ከቆየው የክለቡ ሌጀንድ ፥ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ትምህርቱ እንደወሰደና እና ፖርቱጋላዊው ኮከብ ምሳሌው እንደሆነም ተናግሯል።


ሮናልዶ ለስኬታማነት እጅግ በጣም በመታተር የሚታወቅ ሲሆን ማክቶሚናይም ስነ ልቦናውን ከፍ ለማድረግ የእርሱን መንገድ መከተልን ነው የመረጠው።


የ23 አመቱ አማካይ በእግር ኳስ ውስጥ አዎንታዊ የሆነ ስነ ልቦናን ማዳበር ለስኬታማነት ቁልፉ ነገር መሆኑን የተናገረ ሲሆን የሮናልዶም ስኬታማነት ምስጢር ይህ መሆኑን ተናግሯል።



ከማንቸስተር ዩናይትድ አካዳሚ ያደገው ማክቶሚናይ ፥ ለመጀመሪያ ጊዜ በዋናው ቡድን የመሰለፍ ዕድልን ያገኘው በጆዜ ሞሪንሆ ስር የነበረ ሲሆን አሁን በኦሌ ጉናር ሶልሻየር ስር ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሚባሉ ተጨዋቾች ውስጥ ራሱን ማስገባት ችሏል።

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...