Saturday, March 14, 2020

"ክርስቲያኖ ሮናልዶ የኔ ምሳሌ ነው" ብሩኖ ፈርናንዴዝ

     አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)





በጥር ወሩ የዝውውር መስኮት ማን ዩናይትድን የተቀላቀለው ፈርናንዴዝ በክለቡ ውስጥ ትልቅ አዎንታዊ ለውጥ ማምጣቱን ብዙዎች የሚስማሙበት ሲሆን በቀያይ ሰይጣኖቹ ደጋፊዎች ዘንድም ዝነኛ ሆኗል።

ከስካይ ስፖርትስ ጋር ቆይታ ያደረገው ብሩኖም የዩናይትድ ደጋፊዎች ባደረጉለት አቀባበል መደሰቱን ተናግሮ በስሙ የሚዘምሩለት ነገርም ይበልጥ ደስ እንዳለው ተናግሯል።

በ£47ሚ. ከስፖርቲንግ ሊዝበን ማን ዩናይትድን ከተቀላቀለ አንስቶም በዘጠኝ ጨዋታዎች ላይ መሰለፍ የቻለ ሲሆን ሶስት ግቦችን አስቆጥሮ አራት ኳስ ደግሞ ለግብ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።


ከስካይ ስፖርትስ ጋር በነበረው ቆይታም የሚከተለውን ብሏል
"ከሌላ ሀገር መጥቶ ትልቅ ክለብን ከትልቅ ተጨዋቾች ጋር መቀላቀል ትልቅ ለውጥ አለቅ።ዩናይትድን የመቀላቀል ዕድሉን ሳገኝ ሁለቴ እንኳን ለማሰብ አልሞከርኩም።"


ክርስቲያኖ ሮናልዶ ማን ዩናይትድን ለመቀላቀሉ ትልቅ ምሳሌ እንደሆነውም ተናግሯል።
"ሮናልዶ ለኔ ትልቅ ምሳሌዬ ነው።ሮናልዶ በመመልከት ትጀምርና ከዛ፡የሚጫወትበትን ክለብ ታያለህ።ያ ክለብ ሁሉንም ማሸነፍ እንደሚችል ታያለህ በስተመጨረሻ በዛ ክለብ መጫወት ህልምህ ይሆናል።"



ስለ ደጋፊዎቹ
"ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ደጋፊዎቹ የሰጡኝ ድጋፍ አስደናቂ ነበር።ገና በመጀመሪያ ወ'ሬ ያሳዩኝ ድጋፍ ትልቅ መነሳሻ ሆኖኛል።"

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...