Monday, March 2, 2020

የዕለተ ማክሰኞ ማለዳ ስፖርታዊ ዜናዎች

              አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)



በዩናይትድ ቤት አስገራሚ እንቅስቃሴ እያደረገ ስለሚገኘው ብሩኖ ፈርናንዴዝ የቀድሞው አሰልጣኙ ሲላስ አስተያየት ሰጥተዋል።የስፖርቲንግ ሊዝበኑ አሰልጣኝ "ፈርናንዴዝ ከዚህም በላይ የመስራት አቅም አለው ፥ እንደ እርሱ አይነት ተጨዋች ተመልክቼ አላውቅም" ሲሉ ነው የተናገሩት።
(Goal)





ማንቸስተር ዩናይትድ እንግሊዛዊውን አጥቂ ጄደን ሳንቾ ከማንቸስተር ዩናይትድ የማስፈረም ዕድሉ ከፍተኛ ነው።ቀያይ ሰይጣኖቹ ለ19 አመቱ ተጨዋች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የተጨዋቾች ዝውውር ሪከርድንም እንደሚሰብር ይጠበቃል።
(Telegraph)




ፈረንሳዊው አማካይ ፖል ፖግባ በዚህ ሳምንት ከጉዳቱ አገግሞ ወደ ልምምድ የሚመለስ ሲሆን ብዙዎችም ድንቅ እንቅስቃሴን እያደረገ ካለው ከብሩኖ ፈርናንዴዝ ጋር የሚኖረውን ጥምረት በጉጉት እየጠበቁ ይገኛሉ።
(ESPN)





የአርሰናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ መድፈኞቹ በቀጣዩ አመት በሻምፒዮንስ ሊግ የመሳተፍ ዕድላቸው አናሳ መሆኑን ተከትሎ ፥ አዳዲስ ተጨዋቾችን ማግኘት አዳጋች እንዳይሆንበት እንደሚሰጋ ገልጿል።
(ESPN)





በቡንደስ ሊጋ አስደናቂ እንቅስቃሴ እያደረገ የሚገኘውን የአር.ቢ. ሌብሲሁን ጀርመናዊ አጥቂ ቲሞ ዋርነር ለማዘዋወር ሊቨርፑል እና ማን ዩናይትድ ፉክክር ውስጥ ገብተዋል ፥ የዝውውር ሂሳቡም £100ሚ. ገደማ እንደሚሆን ይጠበቃል።
(Express)




አትሌትኮ ቢልባኦ አርጀንቲናዊውን አጥቂ ጎንዛሎ ሂጎይን ከጁቬንትስ የማዘዋወር ፍላጎት አለው።ሂጎይን በላሊጋው ከዚህ ቀደም ለሪያል ማድሪድ መጫወቱ ይታወሳል።
(Marca)




በማንቸስተር ሲቲ በጥብቅ እየተፈለገ ያለው የኤቨርተኑ እንግሊዛዊ ተከላካይ ሜሰን ሆልጌት ስለ ዝውውር ዜናዎች ተጠይቆ ሙሉ ትኩረቱ ኤቨርተን ላይ እንደሆነ ተናግሯል።
(Mail)





ፍራንክ ላምፓርድ ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባልጋ በስታንፎርድ ብሪጅ እንደሚቆይ ተናገረ።
(Mail)










No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...