ማን ዩናይትድ ዛሬ ከኒውካስትል ጋር በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቦክሲንግ ዴይ ጨዋታ ምን አይነት አሰላለፍ ይከተላል?
ዛሬ በቦክሲንግ ዴይ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዘጠኝ ጨዋታዎች የሚደረጉ ሲሆን በኦልድ ትራፎርድ ማን ዩናይትድን ኒውካስትል ዩናይትድን ያስተናግዳል፡፡
ባለፈው ጨዋታ በዋትፎርድ የተረቱት የኦሌ ጉናር ሶልሻየር ልጆች የዛሬውን ጨዋታ በድል የመወጣት ሀላፊነት ተሰጥቷቸው ወደ ሜዳ ይገባሉ፡፡
በዩናይትድ በኩል በበጎ መልኩ እየተነሳ የሚገኘው የፖል ፖግባ ወደ ሜዳ መመለስ ሲሆን ከሶስት ወራት ጉዳት በኃላ ዛሬ እንደሚሰለፍ ይጠበቃል፡፡
በዛሬው ጨዋታ ከዋትፎርድ ጋር ደካማ የነበረው ዴቪድ ዴሄያ በሮሜሮ ሊተካ እንደሚችልም እየተነገረ ነው፡፡
በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ሴንት ጄምስ ፓርክ ላይ ኒውካስትል ማን ዩናይትድን 1-0 አሸንፎ ነበር፡፡
No comments:
Post a Comment