Monday, December 10, 2018

"ቁጥሮች አይዋሹም -፤ባሎንዶር ለኔ ነበር የሚገባኝ" ሮናልዶ

"ቁጥሮች አይዋሹም -፤ባሎንዶር ለኔ ነበር የሚገባኝ" ሮናልዶ


➡የጁቬንትሱ አጥቂ በዘንድሮው አመት ስድስተኛ ባሎንዶሩን ለማግኘት ተስፋ አድርጎ የነበረ ቢሆንም የቀድሞው የክለብ አጋሩ ሉካ ሞድሪች ማሸነፉ አይዘነጋም ።

ዛሬ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በነበረው ቃለ ምልልስም በዚህ ዓመት የነበረው ባሎንዶር ከሞድሪች ይልቅ ለሱ እንደሚገባ ተናግሯል ።

"እኔ ሁልጊዜም በየአመቱ ባሎንዶርን ማሸነፍ ይገባኛል ፤የምሰራው ለዚህ ነህ ምናልባት ካልተሳካ ግን የአለም ፍፃሜ ነው ማለት አይደለም ።ቁጥሮች አይዋሹም ፤ ይህ ማለት ግን ባላሸነፍ እንኳን በጣም ይከፋኛል ማለት አይደለም ።ምርጥ እና ደስተኛ ጓደኞች እንዲሁም ቤተሰቦች አሉኝ ፤አለም ላይ ባሉ ምርጥ ክለቦች ተጫውቻለሁ ፤ይህንን ባለማሸነፌ ቤቴ ሄጄ የማለቅስ ይመስልሃል ?

"እርግጥ ነው ተከፍቻለው፥ነገር ግን ህይወት ይቀጥላል እኔም ጠንክሬ እየሰራው ነው" በማለት ተናግሯል ሮናልዶ።


ፖርቹጋላዊው ኮከብ በ2018 በ48 ጨዋታዎች 45 ግቦችን ማስቆጠር ችሏል።

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...