Monday, December 31, 2018

የሰኞ ከሰዓት ስፖርታዊ ዜናዎች

°ስሙ በስፋት ከዝውውር ጋር በመያያዝ ላይ የሚገኘው ኢስኮ ሪያል ማድሪድን በጥር ወር የዝውውር መስኮት እንደማይለቅ ተናገረ።ስፔናዊው የ26 አመት አማካይ ስሙ በስፋት ከእንግሊዙ
ክለብ ቼልሲ ጋር ሲያያዝ ነበር።
(Deportes Cuatro, via Metro)


°ማንችስተር ሲቲ የሪያል ቤቲሱን የግራ መስመር ተከላካይ ጁኒየር ፊርፖ ለማዘዋወር ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ቢሆንም ከሪያል ማድሪድ ከፍተኛ ፈተና ገጥሞታል።
 (Mirror)


°የሊቨርፑሉ አጥቂ ዶሚኒክ ሶላንኬ የህክምና ምርመራውን በክሪስታል ፓላስ  በማድረግ ላይ ይገኛል።የ21 አመቱ አጥቂ ወደ ሴል ሀረስት ፓርክ በውሰት ነው የሚዘዋወረው ።
(Mail)


°የ23 አመቱን የሊል ዊንገር ኒኮላስ ፔፔ ለማዘዋወር አርሰናል ፣ባርሴሎና እና ማንችስተር ሲቲ ፉክክር ውስጥ ገብተዋል ።
(Le Voix du Nord, via Star)


°ራፋዔል ቫራን የእግር ኳስ ህይወቱን በሪያል ማድሪድ ለመጨረስ እንደሚያስብ Don Balon አስነብቧል ።ፈረንሳዊው ኢንተርናሽናል ለቡድን አጋሩ ሰርጂዮ ራሞስ ጉዳዩን ነግሮታልም ተብሏል ።


°ቼልሲ የቦሩሲያ ዶርትሙንዱን የአጥቂ አማካይ ክርስቲያን ፑሉሲች በቀጣዩ
የዝውውር መስኮት ለማዛዋወር £45M አሰናድቷል።የጀርመኑ ክለብ ግን
የሌሎችን ክለቦች ፍላጎት በመመልከት አሜሪካዊውን ተጨዋች በተሻለ ገንዘብ
መሸጥ ይፈልጋል።
(ESPN)


°የኒውካስትሉ አሰልጣኝ ራፋ ቤኒቴዝ የሊድስ ዩናይትዱን አጥቂ ኬማር
ለማዛወር አቅደዋል።ቤኒቴዝ ተጨዋቹን ማዘዋወር የሚፋልጉት በጥር ወር
የዝውውር መስኮት ነው።
(Sunday Mirror)


°አዲሱ የማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ኦሊገነር ሶልሻየር ስፔናዊው ግብ
ጠባቂ ዴቪድ ዴሄያ እና ፈረንሳዊውን አንቶኒዮ ማርሻል አዲስ ኮንትራት
እንዲፈርሙለት ይፈልጋል።ለማንችስተር ዩናይትድ የበላይ አመራሮችም
አሳውቋቸዋል።
(Mail on Sunday)


°ጣሊያናዊው የማንችስተር ዩናይትድ ተከላካይ ማቲዮ ዳርሚያን በሴሪያዎቹ
ክለቦች ኢንተር ሚላን እና ላዚዮ ይፋለጋል።
(Calciomercato)


°አርሰናል በቶተንሀም በጥብቅ የሚፈለገውን የኖርዊች ሲቲውን የ18 አመት
ታዳጊ የቀኝ መስመር ተከላካይ ማክስ አሮንስ ለማዘዋወር ጥረት ጀምሯል።
(Sunday Mirror)


°ሊቨርፑል ቱርካዊውን የ19 አመት የአጥቂ አማካይ አብዱልቃድር ኡመር
የማስፈረም ፍላጎት አለው።ሮማ እና ማንችስተር ሲቲም የተጨዋቹ ፈላጊዎች
ናቸዉ ።
(Fotomac, via Star on Sunday)


°የ33 አመቱ የቶተንሀም አጥቂ ፈርናንዶ ሊዮሬንቴ በጥር ወር የዝውውር
መስኮት ወደ ቱርኩ ክለብ ጋላታሳራይ ለመዘዋወር በግሉ ከስምምነት ላይ
ደርሷል።
(Turkish outlet Star, via Sun on)

1 comment:

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...