Saturday, December 29, 2018

የዕሁድ ረፋድ አዳዲስ ስፖርታዊ ዜናዎች

°ቼልሲ የቦሩሲያ ዶርትሙንዱን የአጥቂ አማካይ ክርስቲያን ፑሉሲች በቀጣዩ የዝውውር መስኮት ለማዛዋወር £45M አሰናድቷል።የጀርመኑ ክለብ ግን የሌሎችን ክለቦች ፍላጎት በመመልከት አሜሪካዊውን ተጨዋች በተሻለ ገንዘብ መሸጥ ይፈልጋል።
(ESPN)


°የኒውካስትሉ አሰልጣኝ ራፋ ቤኒቴዝ የሊድስ ዩናይትዱን አጥቂ ኬማር ሩፌ ለማዛወር አቅደዋል።ቤኒቴዝ ተጨዋቹን ማዘዋወር የሚፋልጉት በጥር ወር የዝውውር መስኮት ነው።
(Sunday Mirror)


°አዲሱ የማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ኦሊገነር ሶልሻየር ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴሄያ እና ፈረንሳዊውን አንቶኒዮ ማርሻል አዲስ ኮንትራት እንዲፈርሙለት ይፈልጋል።ለማንችስተር ዩናይትድ የበላይ አመራሮችም አሳውቋቸዋል።
(Mail on Sunday)


°ጣሊያናዊው የማንችስተር ዩናይትድ ተከላካይ ማቲዮ ዳርሚያን በሴሪያዎቹ ክለቦች ኢንተር ሚላን እና ላዚዮ ይፋለጋል።
(Calciomercato)


°አርሰናል በቶተንሀም በጥብቅ የሚፈለገውን የኖርዊች ሲቲውን የ18 አመት ታዳጊ የቀኝ መስመር ተከላካይ  ማክስ አሮንስ ለማዘዋወር ጥረት ጀምሯል።
(Sunday Mirror)


°ሊቨርፑል ቱርካዊውን የ19 አመት የአጥቂ አማካይ አብዱልቃድር ኡመር የማስፈረም ፍላጎት አለው።ሮማ እና ማንችስተር ሲቲም የተጨዋቹ ፈላጊዎች ናቸዉ ።
(Fotomac, via Star on Sunday)


°የ33 አመቱ የቶተንሀም አጥቂ ፈርናንዶ ሊዮሬንቴ በጥር ወር የዝውውር መስኮት ወደ ቱርኩ ክለብ ጋላታሳራይ ለመዘዋወር በግሉ ከስምምነት ላይ ደርሷል።
(Turkish outlet Star, via Sun on
Sunday)



ቁጥራዊ እውነታዎች
⬅️ሮበርቶ ፈርሚንሆ በመጀመሪያው አጋማሽ ባስቆጠራቸው ሁለት ግቦች መሀከል ያለው ልዩነት 90 ሰከንድ ብቻ ነው።

➡️ሮበርቶ ፈርሚንሆ በፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ላይ 8 ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፤ ሮቢ ፎለር በ9 ግቦች በታሪክ ቀዳሚው ተጨዋች  ነው።

➡️ሳዲዮ ማኔ የሊቨርፑልን ማሊያ ለብሶ አርሰናል ላይ 4 ግቦችን አስቆጥሯል ፤ በግሉ ከየትኛውም ክለብ በላይ መድፈኞቹ ላይ በርካታ  ግብ አስቆጥሯል ።

➡️አርሰናል በፕሪሚሪየር ሊግ በአጠቃላይ በመጀመርያው አጋማሽ 4 ግብ ሲቆጠርበት ዛሬ ለአራተኛ ጊዜ ነው፤ ሁለት ጊዜ በሊቨርፑል (2001 በማንችስተር ዩናይትድ ፣2014 በቼልሲ)

➡️የሮበርቶ ፈርሚንሆ ሀት ሪክ በሁለቱ ክለቦች ታሪክ ስድስተኛ ሀትሪክ ነው።

➡️ሙሀመድ ሳላህ በአንድ ጨዋታ ግብ ሲያስቆጥር እና አሲስት ሲያደርግ ከባለፈው አመት ጀምሮ ለ10ኛ ጊዜ ነው።በአውሮፓ አምስቱ ታላቅ ሊጎች የሚበልጠው ኔይማር በ11 ጨዋታዎች ነው።

➡️ሮበርቶ ፈርሚንሆ በፕሪሚየር ሊግ ከሮቢንሆ እና አፎንሶ አልቬዝ በኃላ ሀትሪክ የሰራ በሶስተኛው ብራዚላዊ ሆኗል።

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...