Saturday, December 1, 2018

ትላልቅ ተጨዋቾችን ማስፈረም አስቸጋሪ ነው - ሞሪንሆ

"ትላልቅ ተጨዋቾችን መግዛት በተለይ ለማንቸስተር ዩናይትድ ከባድ ነው " ሞሪንሆ


ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ፕሪሚየር ሊጉ ላይ ፉክክሩ በማየሉ ምክንያት ትላልቅ ተጨዋቾችን ማዘዋወር አዳጋች እንደሆነ ተናገሩ።
የቀያይ ሰይጣኖቹ አለቃ ከአመት አመት ትላልቅ ተጨዋቾችን የማስፈረም ጉዳይ በተፎካካሪዎች መጨምር ምክንያት ከባድ ነው ብለዋል ።


ማንቸስተር ዩናይትድ በዘንድሮው አመት ከ13 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ስድስቱን ብቻ ያሸነፈ ሲሆን ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል ፤ ይህ ደግሞ አሰልጣኙ ላይ ጫናን አሳድሯል ።

አወዛጋቢው አሰልጣኝ ይህንን አስተያየት የሰጡት በክለባቸው ቀውስ ምክንያት ደጋፊዎች በጥር ወር የዝውውር መስኮት ተጨዋቾች እንዲመጡ ጫና እያሳደሩ መሆኑን ተከትሎ ነው።


ዛሬ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቸስተር ዩናይትድ ሳውዝሀምተንን ይገጥማል ።

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...