Tuesday, December 8, 2020

የዕለተ ማክሰኞ ከሰዓት ስፖርታዊ ዜናዎች

የሀገር ውስጥ 

Saint George S.A
አማኑኤል ገ/ሚካኤል ፈረመ
==========//===========
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኅዳር 27 ቀን 2013 ዓ.ም ባደረገው የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ በመቀሌ የሚገኙት 3 ክለቦች ተጫዋቾች ለ2013 ዓ.ም ብቻ በፈለጉት ክለብ ተመዝግበው እንዲጫወቱ በወሰነው መሰረት ታዋቂው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች አማኑኤል
ገ/ሚካኤል ለክለባችን ለመጫወት ፊርማውን አኑሯል፡፡
በዛሬው እለት የኮቪድ 19 ምርመራውን ካከናወነ በኋላ ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ቢሾፍቱ ይድነቃቸው ተሰማ የወጣቶች እግር ኳስ አካዳሚ በመግባት ቡድኑን የሚቀላቀል መሆኑ ታውቋል፡፡
(Saint George F.C)



ከውጭ 






ዛሬ ምሽት ወደ ቀጣዩ ዙር አላፊውን የሚወስኑ ፤ የሻምፒዮንስ ሊግ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ይደረጋሉ 

በምድብ H ፤ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ፓሪሰን ዤርመን ከ ኢስታንቡል ባሳኽሲር እና ሌብዚኽ ከ ማን ዩናይትድ ይጫወታሉ።እዚህ ምድብ ላይ ከኢስታንቡል ባሳኽሲር ውጪ ያሉት ክለቦች ዕኩል ዘጠኝ ነጥብ ስላላቸው በጣም ተጠባቂ ሆኗል ።

በምድብ G ደግሞ ሁለቱ ማለፋቸው ያረጋገጡት ባርሴሎና እና ዩቬንትስ ይጋጠማሉ።ሜሲ እና ሮናልዶም ከረዥም ጊዜ በኋላ ይገናኛሉ።

የሁሉም ጨዋታዎች መርሃግብር ፡

ቼልሲ ከ ክራስኖዳር [5:00]
ሬንስ ከ ሲቪያ [5:00]

ላዚዮ ከ ክለብ ብሩዥ [2:55]
ዜኒት ፒተርስበርግ ከ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ [2:55]

ባርሴሎና ከ ዩቬንትስ [5:00]
ዳይናሞ ኪዬቭ ከ ፌረንክቫሮስ [5:00]

ፓሪሰን ዤርመን ከ ኢስታንቡል ባሳኽሲር [5:00]
ሌብዚኽ ከ ማን ዩናይትድ [5:00]




 "ፖግባ ከማን ዩናይትድ ጋር የነበረው ጊዜ አብቅቷል" ሚኖ ራዮላ

በዚህ ሲዝን በኦልድትራፎርድ ከባድ ጊዜን እያሳለፈ የሚገኘው ፖል ፖግባ ከማን ዩናይትድ እንደሚለቅ አነጋጋሪ የሆነው ወኪሉ ሚኖ ራዮላ ተናገረ ።ከTuttosport ጋር ቆይታ የነበረው ራዮላ ስለ ፖግባ ቀጣይ የኦልድትራፎርድ ቆይታ ሲጠየቅ "አብቅቷል" ሲል ነው የመለሰው ።

እስከ 2022 በቲያትር ኦፍ ድሪምስ የሚያቆይ ኮንትራት ያለው ፖግባ በተለይ ከቀድሞው ክለቡ ዩቬንትስ ጋር ስሙ በስፋት ሲያያዝ ቆይቷል።

ፖግባ በዚህ አመት በሁሉም የውድድር አይነቶች 13 ጊዜ የተጫወተ ሲሆን ስድስት ጊዜ ብቻ ነው ቀዳሚ ተሰላፊ የነበረው።





 ሁለቱ የሴሪያ ክለቦች የሆኑት ጁቬንቱስ እና ኢንተር ሚላን የፒኤስጂውን አርጀንቲናዊውን  ኮከብ አንሄል ዲማሪያን በክረምት ለማስፈረም ፉክክር ውስጥ መግባታቸውን  Calcio  Mercato አስነብቧል። ፒኤስጂዎች እስካሁን ለተጨዋቹ ኮንትራት ያላቀረበለት ሲሆን ልጁም በክረምት ክለቡን ለመልቀቅ መዘጋጀቱ ታውቋል። 




አርጀንቲናዊው የጁቬንቱስ ኮከብ ፓብሎ ዲባላ በተለያዩ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ራዳር ውስጥ መግባቱን 90min አስነብቧል።በጁቬ ተጨማሪ ኮንትራት ያለው ዲባላ አሁን ላይ በፒርሎ ስር ደስተኛ እንዳልሆነ የተነገረ ሲሆን በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ማቅናቱ አይቀሬ ሆኗል። 





አርሰናሎች የማንችስተር ሲቲውን እንግሊዛዊውን  የመሀል ተከላካይ ጆን ስቶንስን ለማስፈረም አንደሚፈልጉ 90min ያስነበበ ሲሆን አርሰናሎች ልጁን በጥር ለማምጣት ይፈልጋሉ። ስቶንስ በማንችስተር ሲቲ እስከ 2022 ኮንትራት ያለው ሲሆን ማንችስተር ሲቲዎች የተጨዋቹን ኮንትራት ለማራዘም ፍላጎት የላቸውም። 





ማንችስተር ዩናይትዶች በቀጣይ ክረምት ዝውውር አሮዋን ቢሳካን ሚፎካከር የቀኝ መስመር ተከላካይ አንደሚያስፈርሙ M.E.N አስነብቧል።ዩናይትዶች አሁን ላይ ዋነኛ ትኩረታቸው የአትሌቲኮ ማድሪዱ ኬራን ትሪፒየር ሲሆን የሱ ዝውውር ማይሳካ ግን የሪያል ማድሪዱን ቫስኩዌዝን ለማምጣት እቅድ አላቸው። 





ኤሲ ሚላኖች በጥር የዝውውር መስኮት ተጨማሪ ተከላካይ ለማስፈረም ወደ ገበያው እትደሚወጡ አሰልጣኙ ይፋ ሲያደርጉ በጥርም የዝውውር መስኮት የመጀመሪያ እቅዳቸው የቶተንሀሙ ዳቪድሰን ሳንቼዝ መሆኑ The Sun ያስነበበ ሲሆን ሚላኖች ልጁን በውሰት አልያም በቋሚ ዝውውር ልጁን ለመውሰድ ዝግጁ ናቸው። 





በዚህ አመት ኮንትራቱ ከአርሰናል ጋር የሚጠናቀቀው ጀርመናዊው አማካይ ሜሱት ኦዚል በቀጣይ አመት ወደ ትልቅ ክለብ ለማምራት ዝግጁ እንደሆነ The Mirror ያስነበበ ሲሆን ወደ የትኛው ሊግ ማምራት እንደሚፈልግ ግን እስካሁን አልታወቀም። 




በጁቬንቱስ ቦታ እንደሌለው የተነገረው እና  በዚህ አመት ኮንትራቱ የሚጠናቀቀው ሳሚ ከዲራ በጥር የዝውውር መስኮት የተለያዩ የቻምፒዮንስ ሺፕ ክለቦች ለማስፈረም ፍላጎት አሳይተዋል።ተጨዋቹ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች መሄድ ቢፈልግም ዋትፎርድ ፣በርንማውዝ እና ኖርዊች ተጨዋቹን ለመውሰድ ፍላጎት አላቸው። 





ቸልሲዎች እንግሊዛዊውን ካሉም ሁድሰን ኦዶይን እንደማይለቁት ይፋ አድርገዋል። ለተጨዋቹ ኮንትራት ቢያቀርቡለትም ለመፈረም ፍላጎት አቷ። ነገር ግን ልጁን ቸልሲዎች አሳልፈው ለመስጠት አይፈልጉም ፤ ኦዶይ በሙኒክ በጥብቅ ይፈለጋል።

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...