Sir King Kenny Daglish
ስለ ስቴቨን ዤራርድ ታማኝነት አንድሪያስ ፒርሎ የተናገረው
"በሚላን እያለሁ አንቾሎቲ ወደ እኔ መጣ እና 'ስቴቨን ዤራርድን ላስፈርመው አስቢያለሁ።ካንተ ጋር መሀል ላይ ትጣመራላችሁ ምን ታስባለህ' አለኝ "
እኔም "በጣም ጥሩ ሀሳብ ነው አስፈርመው።" አልኩት
በዚያ ጊዜ ዤራርድ በአውሮፓ ሙሉዕ የሚባል ድንቅ አማካይ ነበር።ስለዚህ እኔም ከእርሱ ጋር አብሮ መጫወትን ፈልጌ ነበር።ከዚያ ከሳምንታት በኋላ ካርሎን ዝውውሩ ምን ሂደት ላይ እንዳለ ስጠይቀው ዤራርድ 'አይሆንም ፤ ከሊቨርፑል ጋር አልለያይም' እንዳለው ነገረኝ።
በዚያን ጊዜ ሚላን የአውሮፓ ሻምፒዮን የነበረ ሲሆን ምርጥ ስብስብም የነበረው ቡድን ነበር።ዤራርድ ለሊቨርፑል በጣም ታማኝ ነበር።"
No comments:
Post a Comment