Tuesday, November 3, 2020

የዕለተ ማክሰኞ ከሰዓት ስፖርታዊ ዜናዎች

                      አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)


 ኢንተር ሚላን ዴንማርካዊውን አማካይ ክርስቲያን ኤሪክሰን ከመሸጥ ይፈልጋል።£18ሚ. የዝውውር ዋጋው እንደሚሆን የተነገረውን ኤሪክሰን ኤሲ ሚላን ፣ ሮማ እና ላዚዮ ይፈልጉታል።

(Calciomercato - in Italian)







ብራዚላዊው ኢንተርናሽናል ኔይማር በፓሪሰን ዤርመን መቆየት እንደሚፈልግ ለአመራሮቹ ነግሯቸዋል።የ28 አመቱ አጥቂ እስከ 2022 የሚያቆይ ኮንትራት ያለው ሲሆን ከወዲሁ ንግግር ጀምሯል።

(Foot Mercato, via Sunday Mirror)






እንግሊዛዊው ተከላካይ ፊል ጆንስ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት በውሰት ከማን ዩናይትድ ወደ በርንሌይ እንደሚጓዝ ዴይሊ ስታር አስነብቧል።

(Daily Star Sunday)






የሪያል ማድሪዱ ስፓኒያርድ ኢስኮ ከቀድሞው አሰልጣኙ ካርሎ አንቾሎቲ እና የቡድን አጋሩ ሀሜስ ሮድሪጌዝ ጋር በኤቨርተን ሊገናኝ ይችላል በቀጣዩ የዝውውር መስኮት።

(Sunday Mirror)






ቦሲኒያ ሄርዞጎቪኒያዊውን ተከላካይ አነል አህመድሆድዚኽ ለማዘዋወር ቼልሲ ለማልሞ £8ሚ. አቅርቧል።

(Expressen - in Swedish)






የቀድሞው ፈረንሳዊ የአርሰናል አጥቂ ሮበርት ፒሬዝ ኪልያን ምባፔ ወደ ሪያል ማድሪድ ቢጓዝ የእግር ኳስ ሕይወቱ የተሻለ እንደሚሆን መክሯል።

(Goal)






በአመቱ መጨረሻ በናፖሊ ያለው ውል የሚያበቃው ጄናሮ ጋቱሶ አዲስ ኮንትራት ሊፈራረም ነው።ጋቱሶ በዚህ አመት ጥሩ ቡድን ሰርቷል።

(Sky Italia - in Italian)






ዲዬጎ ሲሞኒ ለሊውዝ ሱዋሬዝ አጣማሪ የሚሆን አጥቂ እየፈለገ ሲሆን ዋነኛው ዕቅዱ ደግሚ የአታላንታው ዱቫን ዛፓታ ነው።

(Calciomercato - in Italian)







አሁን ክለብ አልባ የሆነው የቀድሞው የዩቬንትስ ፣ አትሌቲኮ ማድሪድ እና ባየርን ሙኒክ አጥቂ ማሪዮ ማንዙኪች ከአስቶን ቪላ የቀረበለትን የዝውውር ጥያቄ ውድቅ አድርጓል።

(Birmingham Mail)

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...