አቅራቢ - ኢብራሒም ሙሐመድ
አርሰናሎች አይናቸውን ወደ ኒውካስትሉ ግብ ጠባቂ ዎድማን ላይ ጥለዋል። እንደ ዘገባው ከሆነ በውሰት በቻምፒዮን ሺፑ በስዋንሲ ድንቅ ጊዜ እያሳለፈ የሚገኘውን ግብ ጠባቂ አርቴታ በክረምቱ በማዘዋወር ከበርናንድ ሌኖ ጋር ለማፎካከር እንደፈለጉ ተሰምቷል።
ቸልሲ እና ኢንተር ሚላን በአንድ ተከላካይ ላይ ተፋጠዋል።ተጨዋቹም የ20 አመቱ የሄላስ ቬሮናው ማራሽ ኩምቡላ ነው ፥ እንደ ላአሬና ዘገባ ከሆነ ቸልሲ ለተጨዋቹ እስከ £21m ለመክፈል ፍቃደኛ ናቸው።
ባየርን ሙኒኮች አንድሬ ቴርስቴገንን ከባርሴሎና ለማስፈረም የአለም የበረኞች ሪከርድን ለመስበር ይፈልጋሉ።እንደ ዴይሊ ሚረር ዘገባ ከሆነ ተጨዋቹ ሙኒኮችን እስከ £91m ያስወጣቸዋል ተብሏል። እስቴገን በ2014 ከጀርመኑ ክለብ ሞንቼ ግላድባህ መፈረሙ ይታወሳል።
ሊቨርፑሎች የቫሌንሲያውን ፌራን ቶሬስን ለማስፈረም ንግግር ጀምረዋል። ተጨዋቹ ከስፔኑ ሀያላን ክለቦች ባርሴሎና እና ሪያል ማድሪድ ቢፈለግም ሊቨርፑሎች ልጁን ለማስፈረም ገፍተው መተዋል።
ሪያል ማድሪዶች ኮንትራቱ በ2021 የሚጠናቀቀውን ሁለገቡን የ28 አመቱን ስፔናዊ ሉካስ ቫዝኬስን በክረምት ለመልቀቅ ዝግጁ ናቸው። እንደ AS ዘገባ ከሆነ ማድሪዶች ለተጨዋቹ አዲስ ኮንትራት ለመስጠት ምንም ፍላጎት የላቸውም። ይህን ተከትሎ ልጁን በቀጣይ አመት በነፃ ላለማጣት ሲሉ በክረምት ለመልቀቅ ዝግጁ ናቸው።
ሌስተር ሲቲዎች በክረምት ጂሚ ቫርዲ ክለቡን ሚለቅ ከሆነ በሊግ አንድ በዘንድሮ የውድድር አመት 12 ጎል እና 3 አሲስት ያረገውን የሜትዙን አጥቂ ሀቢብ ዲያሎን ማስፈረም ይፈልጋሉ።ተጨዋቹ ከሌስተር በተጨማሪ በሊድስ፣በቸልሲ እና በክርስቲያል ፓላስ ይፈለጋል።
አትሌቲኮ ማድሪዶች በበርካታ ክለቦች አይን ውስጥ የወደቀውን ቶማስ ፓርቲን ለተጨማሪ አመታት ለማቆየት አዲስ ኮንትራት አቅርበውለታል።
No comments:
Post a Comment