Thursday, July 4, 2019

የሀሙስ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

ዕለተ ሀሙስ ምሽት የወጡ የሀገር ውስጥ እንዲሁም የባህር ማዶ ስፖርታዊ መረጃዎች

      አዘጋጅ እና አቅራቢ - አብዱልቃድር በሽር (የሪሐና ልጅ)

የሀገር ውስጥ ዜናዎች

⇉በዘንድሮ አመት ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚሰናበቱት ሶስቱም ክለቦች በስተመጨረሻ ታውቀዋል።አስቀድሞ መውረዱን ካረጋገጠው ደደቢት ጋር የሚወርዱት ሁለት ክለቦችን ለማወቅ እስከትናንትናዋ ዕለት ድረስ የእግር ኳስ ቤተሰቡ ለማወቅ ጊዜ የወሰደበት ቢሆንም በስተመጨረሻ እነዚህ ሁለት ክለቦች አንጋፋው ክለብ መከላከያ እና ደቡብ ፖሊስ መሆናቸው እውን ሆኗል።
በዚህም መሰረት ደደቢት ፥ መከላከያ እና ደቡብ ፖሊስ ከ2011 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መሰናበታቸው ከወዲሁ ተረጋግጧል።በቀጣዩ አመት እነዚህን ክለቦች በመተካት ወደ ሀገሪቱ ቁንጮ ሊግ የሚመጡት ወልቂጤ ከነማ ፥ ሀዲያ ሆሳዕና እና ሰበታ ከነማ መሆናቸው ከሳምንታት በፊት መረጋገጡ የሚታወስ ነው።






⇉ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን ጋር ያለው እሰጣ እገባ አንጋፋውን ክለብ ከሊጉ እንዲወጣ ምክንያት ሊሆነው ይችላል የሚል ሀሳብ በበርካታ የእግር ኳስ ቤተሰብ ዘንድ እየተነሳ ይገኛል።የ83 አመታት ዕድሜ ያለው ቅዱስ ጊዮርጊስ ትናንት ከፋሲል ከነማ ጋር ላለበት ጨዋታ ከዚህ ቀደም የነበረውን መርሃ ግብር  ሳያደርግ ወደ ጎንደር እንደማይጓዝ ቀድሞ ለፌድሬሽኑ ያሳወቀ ቢሆንም አወዛጋቢው ፌድሬሽን ግን ክለቡ በፎርፌ እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል።
ይህንን ውሳኔም ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና ውሳኔው ተገቢ እንዳልሆነ እና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር እንደሚቆም አስታውቋል።ሁለቱ ሰፊ ህዝባዊ የደጋፊ መሰረት ያላቸው የመዲናዋ ብሎም የሀገሪቱ ጉምቱ ክለቦች በቀጣዩ አመት ከሌሎች በተለያየ እርከን ላይ ካሉ 20 የአዲስ አበባ ክለቦች ጋር በመሆን የራሳቸውን ሊግ ሊመሰርቱ ሽር ጉድ ላይ እንዳሉም እየተነገረ ነው።





የባህር ማዶ ዜናዎች



✔️ናቾ ሞንሪያል ከአርሰናል ጋር ለተጨማሪ አምድ አመት የሚያቆየውን ኮንትራት ፈርሟል።የ33 አመቱ ስፔናዊ የግራ መስመር ተከላካይ ወደ ሀገሩ ክለቦች ሊመለስ እንደሆነ ሲነገር የቆየ ቢሆንም በስተመጨረሻ ለሰባተኛ ተከታታይ አመት ከመድፈኞቹ ጋር ለመሰንበት ከስምምነት ላይ ደርሷል።አርሰናል ይህንን የኮንትራት ማራዘሚያ ማምሻውን እንደሚያዳውቅ ይጠበቃል።

(THE SUN)








|ይፋዊ|⇉⇉ ፍራንክ ላምፓርድ የቼልሲ አሰልጣኝ ሆኖ ተሹሟል።የቀድሞው የሰማያዊዎቹ አማካይ በደርቢ ካውንቲ የአንድ አመት ቆይታ ካደረገ በኋላ ነው ማውሪዚዮ ሳሪን በመተካት ስታንፎርድ ብሪጅ የከተመው።ላምፓርድ በተጨዋችነት ታሪክ የሰራበትን ክለብ በአሰልጣኝነት ለሶስት አመታት ለማገልገል ከስምምነት ላይ ደርሶ ኮንትራትም ተፈራርሟል።
ፍራንክ ላምፓርድ በተጨዋችነት ዘመኑ 13 አመታትን በሰማያዊዎቹ ቤት ያሳለፈ ሲሆን 649 ጊዜ ተሰልፎ 211 ግቦችን ከመረብ ላይ ማሳረፉ ይታወሳል።
(official chelsea fc)






|ይፋዊ|⇉⇉ ማን ሲቲ ሮድሪን በክለቡ ሪከርድ ዋጋ €70M አስፈረመ።የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮኖች የ23 አመቱን ስፔናዊ ኢንተርናሽናል ከአትሌቲኮ ማድሪድ ያስፈረሙት የውል ማፍረሻውን በመክፈል ነው።ስፔናዊው አማካይ በኤቲሀድ ለአምስት አመታት የሚያቆየውንም ኮንትራት ፈርሟል።
(official man city fc)





|ይፋዊ|⇉⇉ አትሌቲኮ ማድሪድ የቤኔፊካውን ታዳጊ ኮከብ ጁዋዎ ፌሊክስ በ€126M አስፈረመ።አትሌቲኮ በተለይ በማን ሲቲ በጥብቅ ሲፈለግ የነበረውን የክንፍ አጥቂ ያስፈረመው በክለቡ ሪከርድ ዋጋ ሲሆን ብዙዎች ግን ዋጋው እጅግ የተጋነነ መሆኑን እየተናገሩ ነው።የ19 አመቱ ፖርቱጋላዊ ከሲቲ በተጨማሪ በማን ዩናይትድ ፥ በጁቬንትስ ፥ በባርሴሎና እንዲሁም በሪያል ማድሪድ በጥብቅ ይፈለግ ነበር።
(official Athletico Madrid)






✔️ዴቪድ ዴሄያ ለቅድመ ውድድር ዝግጅት ወደ ማን ዩናይትድ ተመልሷል።እስከ 2020 ብቻ በኦልድ ትራፎርድ የሚያቆይ ኮንትራት ያለው ስፓኒያርዱ ግብ ጠባቂ ስሙ ከሌሎች ክለቦች ጋር ቢያያዝም ቀያይ ሰይጣኖቹ አሁንም በክለቡ እንዲቆይ እየሞከሩ ነው ።የኢድ ውድ ዋርድ አስተዳደር ለተጨዋቹ አዲስ ኮንትራት ከሳምንታዊ £350,000 ደሞዝ ጋርም ሊያቀርብለት ተሰናድቷል።

(Manchester Evening News)



✔️ሊቨርፑል ሎቭረንን በክለቡ ለማቆየት እየሰራ ነው።የጣሊያኑ ኤሲ ሚላን በዚህ የዝውውር መስኮት ለማዘዋወር ካቀዳቸው ተጨዋቾች አንዱ የሆነውን ዲያን ሎቭረን ሊቨርፑል በክለቡ ለማቆየት እየሰራ ነው።

የ29 አመቱ ክሮሺያዊ በዘንድሮ አመት በአስደናቂው የቨርጅል ቫን ዲክ እና ጆይል ማቲፕ ጥምረት ምክንያት 11 ጨዋታዎች ላይ ብቻ ነው በፕሪሚየር ሊግ የመሰለፍ ዕድል በክሎፕ ተሰጥቶት የነበረው።
(Sky Sports)



✔️የቀድሞው የአርሰናል ሌጀንድ ኢያን ራይት አርሰናል ፔር ኤምሪክ ኦባማያንግን አሊያም አሌክሳንደር ላካዜትን የሚሸጥ ከሆነ ትልቅ ኪሳራ ነው ሲል ተናገረ።ኢያን ራይት ይህንን ያለው ሁለቱ አጥቂዎች ከመድፈኞቹ ጋር ለመለያየት ከጫፍ መድረሱ እየተነገረ በመሆኑ ነው።

(Goal)





✔️በሪያል ማድሪድ በግሉ ታሪኩን በወርቅ ብዕር ያሰፈረው ብታዚላዊው የግራ መስመር ተከላካይ ማርሴሎ በስተ መጨረሻ ከሎስብላንኮዎቹ ጋር ሊለያይ ተቃርቧል።ዕድሜው ሰላሳዎቹን የተሻገረው ማርሴሎ በጁቬንትስ ፥ በአርሰናል፥ በፓሪሰን ዤርመን እና ኤሲ ሚላን ይፈለጋል።
(Sport)



✔️ጁቬንትስ ማቲያ ደ ላይትን ለማዘዋወር ለክለቡ አያክስ €75M አቅርቧል።ሆላንዳዊው ተከላካይ ወደ አሮጊቷ የመሄዱ ነገር አይቀሬ ይመስላል።

(Sky Sports)

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...