Wednesday, July 17, 2019

የረቡዕ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

የረቡዕ ምሽት ስፖርታዊ ዜናዎች

አቅራቢ - ኢብራሒም መሐመድ


አርሰናል ብራዚላዊውን ኤቨርተንን ለማስፈረም ተስማምቱዋል የሚል ዜና ወጥቷል።ለግሬሚዮ ሚጫወተውን ኤቨርተንን ለማስፈረም አርሰናል 36ሚፓ ከፍሎ ለማምጣት ፎክስ ስፖርት የሚባል ድረ-ገፅ ዘግቧል 25ሚፓ ዋና የዝውውር ሂሳብ ሲሆን 10ሚፓ ደግሞ ብቃቱ እየታየ የሚጨመር ይሆናል




ፒኤስጂዎች የ23 አመቱን ፈረንሳዊ ተከላካይ አብዱ ዲያሎን ከቦሩሲያ ዶርትመንድ ማስፈረሙ ተረጋግጧል ለልጁም ለዶርትመንድ 20ሚፓ ያወጣ ሲሆን በፒኤስጂም አምስት አመት የሚያቆየውን ኮንትራት ፈርሟል




በቅርቡ ራፋ ቤኒቴዝን ያሰናበቱት ኒውካስትል ዩናይትዶች በፕሪሚየር ሊጉ በማሰልጠን ብዙ ልምድ ያላቸውን ስቲቭ ብሩስን ከሰአታት በፊት አሰልጣኝ አድርገው መሾማቸውን ይፋ አድርገዋል





አርሰናሎች የሪያል ማድሪዱን ዳኒ ሴቫዮስን በውሰት ለማስፈረም ከማድሪድ ጋር ንግግር እያደረጉ ነው በቀጣይ ቀናትም ጥያቄያቸው ተቀባይነት የሚያገኝ ከሆነ በአንድ አመት የውሰት ውል ወደ ኢምሬት እንደሚመጣ  ተነግሯል







የሌስተሩ አሰልጣኝ ብሬንዳን ሮጀርስ ከማንቸስተር ዩናይትድ እና ማንችስተር ሲቲ ለሀሪ ማጉዋየር የመጣ እሱን የማይመጥን ውል ሁለት ጊዜ ውድቅ እንዳደረጉ ተገለፀ።





አርሰናል የ33አመቱን ፈረንሳዊ ተከላካይ ኮሼልኒ ለመሸጥ ፍቃደኛ መሆኑ ስካይ ስፖርት ዘግቧል ልጁ ወደ ትውልድ ሀገር ተመልሶ መጫወት ይፈልጋል ከአርሰናል ጋር የአንድ አመት ውል ቢቀረውም አርሰናልን በነፃ ነው መልቀቅ ሚፈልገው ለልጁም ተገቢውን ክፍያ ካገኙ እንደሚለቁት ታውቋል የፈረንሳዩ ሊዮን እና ማርሴይ የልጁ ፈላጊ ክለቦች ናቸው




ኤቨርተኖች አዴሞላ ሉክማንን ለአርቢ ሌብዢግ በ 22.5 ሚሊየን ፓውንድ ለመሸጥ ተስማምተዋል ዝውውሩ በ 24 ሰዓት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይገመታል





የጀርመኑ አርቢ ሌብዢክ የፓሪሰን ዤርሜኑን ክሪስቶፈር ንኩኩን ለማስፈረም ከጫፍ ደርሰዋል በጀርመኑም ክለብ አምስት አመት የሚያቆየውን ውል ይፈርማል




የፈረንሳዩ ክለብ ሬንስ የሳውዛንብተኑን የመስመር ተጨዋች ሱፍያን ቦፉልን ለመስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል ለዝውውሩ እስከ €10m የሚከፍሉ ሲሆን በጥቂት ቀናት ውስጥ ዝውውሩ እንደሚጠናቀቅ ተነግሯል





አስቶን ቪላዎች ቤልጂየማዊውን የ ስቴድ ሬይምስ የመሀል ተከላካይ ግልፅ ባልተደረገ ሂሳብ ማዘዋወራቸውን ይፋ አድርገዋል





ሮማዎች የፊዮሬንቲናውን ጆርዳን ቬሬታውትን ለማስፈረም ከጫፍ ደርሰዋል ሮማ ለልጁ €17 + €2ቦነስ የሚከፍሉ ይሆናል ዝውውሩንም ለመጨረስ ትናንት የመጨረሻ ድርድር ማድረጋቸው ታውቋል

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...