Wednesday, November 28, 2018

የሀሙስ ረፋድ የዝውውር ዜናዎች

የሀሙስ ረፋድ የዝውውር ዜናዎች 

ቺሊያዊው ኢንተርናሽናል አሌክሲስ ሳንቼዝ በጥር ወር የዝውውር መስኮት ከማንቸስተር ዩናይትድ ሊሰናበት እንደሚችል እየተዘገበ ነው።የ29 አመቱ አጥቂ ከአርሰናል ከተዘዋወረ አንስቶ በቀያይ ሰይጣኖቹ ቤት ስኬት ርቆታል። በዚህም ምክንያት ከክለቡ የመልቀቅ ፍላጎት ያለው ሲሆን ሞሪንሆም ቢለቅ አይሰፉም። 
(ሚረር)



በውድድሩ አመት መጨረሻ ውሉ የሚያልቀው የቶተንሀሙ አማካይ ሙሳ ዴምቤሌ በበርካታ ክለቦች ይፈለጋል ።በዋናነት የጣሊያኖቹ ጁቬንትስ እና ኢንተርሚላን የ31 አመቱ ቤልጄሚያዊ ፈላጊዎች ናቸው።
(ካልሺዮ መርካቶ)



ባየርን ሙኒክ በጥር ወር የዝውውር መስኮት የቼልሲውን ከ17 አመት በታች የአለም ዋንጫ አሸናፊ ካለም ሁድሰን ኦዶው ለማዘዋወር ከአሁኑ እየሰራ ነው
(ሜል)


ስዊዘርላንዳዊው አማካይ ዠርደን ሻኪሪ በሊቨርፑል ደስተኛ እንደሆነ ተናገረ።የ27 አመቱ ተጨዋች በዠርደን ክሎፑ ቡድን ውስጥ በቋሚነት የመሰለፍ ዕድል ማግኘትን ባይችልም መቆየት እንደሚሻ ነው የተናገረው ።የጣሊያኑ ኢንተር ሚላን የተጨዋቹ ቀንደኛ ፈላጊ ነው።
(ላጋዜታ ዴሎ ስፖርት)



ኒውካስትል ዩናይትድ የ24 አመቱ የአታላንታ ተጨዋች ሚጉዌል አልሚሮን ለማዘዋወር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል ።ፓራጓዊው አማካይ በጣሊያን አስደናቂ ብቃቱን በማሳየት ላይ ይገኛል ።
(ሜል)


    በዘንድሮው አመት በፕሪሚየር ሊጉ አስደናቂ ጊዜን እያሳለፉ ካሉ ክለቦች ዋነኛው ኤቨርተን ነው።አሰልጣኙ ማርኮ ሲልቫም ይህንን ለማጠናከር የ25 አመቱን የዋትፎርድ አማካይ አቡዱላሂ ዶኮሬ ወደ ቪካሬጅ ሮድ ለማምጣት እየሰሩ ነው።
(ሚረር)



ከዝውውር ውጪ ያሉ መረጃዎች 

- ትናንት በሻምፒዮንስ ሊግ ግብ ማስቆጠር የቻለው አርጀንቲናዊው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ በሻምፒዮንስ ሊግ ታሪክ በአንድ ክለብ በርካታ ግብ ያስቆጠረ ተጨዋች ሆኗል 

-ከትናንት በስቲያ በሻምፒዮንስ ሊግ ጁቬንትስ ቫሌንሲያን 1ለ0 ማሸነፉ ይታወቃል ።በጨዋታው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በሻምፒዮንስ ሊግ በግሉ 100 ጨዋታዎችን በማሸነፍ የመጀመሪያው ተጨዋች ሆኗል ።

No comments:

Post a Comment

"ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል

 "ቱሪን አሁንም በልቡ ውስጥ አለ" ራዮላ ፖግባ ወደ ዩቬንትስ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል የፈረንሳዊው ኮከብ ፖል ፖግባ ወኪል የሆነው ሚኖ ራዮላ ፤ አማካዩ በክረምት የዝውውር መስኮት ወደ ቱሪን ሊመለ...